የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

በሰሜን አሜሪካ ተተኪ ካህናትን በበቂ ሁኔታ የማፍራት ሂደት ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) ገለጹ።

August 31, 2023

ነሐሴ ፳፬ ቀን ፳፻ ፲፭ ዓ.ም
******
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰሜን አሜሪካን በሲራኪዮስ ከተማ በምትገኘው የገነተ ደናግል ቅድስት አርሴማ ወክርስቶስ ሰምራ ገዳም ተገኝተው በገዳሙ የአብነት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ለቆዩ አራት ተማሪዎች የዲቁና ማእረግ በመስጠት አባታዊ መመሪያን አስተላልፈዋል።
ገዳሙ በ፳፻፬ ዓ/ም በሥርዓተ ቤተክርስቲያን የተገደመና በሰሜን አሜሪካን ዘርፈ ብዙ አገልግሎት እየሰጠ ያለ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመጀመሪያው ገዳም ነው።

ገዳሙ በሰሜን አሜሪካ የሚገኙ ምዕመናን፣ ካህናትና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ወጣቶች ሠፊ መንፈሳዊ አገልግሎት የሚያገኙበትና በታመሙና በተጨነቁ ጊዜ ሁሉ ወደ ገዳሙ በመጓዝና ሱባኤን በመያዝ እግዚአብሔርን በመማጸን መንፈሳዊ ፈውስን ከእግዚአብሔር የሚቀበሉት ቅዱስ ስፍራ ነው። ሕጻናትና ወጣቶችም በገዳሙ አድገውና የቤተክርስቲያንን የአብነት ትምህርትቶች ተምረው ለነገዋ ቤተክርስቲያን ተተኪ አገልጋዮች የሚሆኑበት እድልም ተፈጥሯል። በማኅበራዊ ዘርፍም በልዩልዩ ምክንያቶች መግባባት የተሳናቸውና የተጋጩ ምዕመናን በሽምግልና ችግሮቻቸውን የሚፈቱበት ሁኔታም በገዳሙ ተመቻችቶ ውጤታማ ሥራ እየተሠራ ይገኛል።

ገዳሙ የሰሜን አሜሪካ ሥልጣኔ የሚፈጥራቸውን በጎ ያልሆኑ ተጽዕኖዎች ተቋቁሞ ከፓለቲካዊና ዘረኝነት አስተሳሰብ በጸዳ መልኩ አገልግሎቱን በመፈጸም ረገድ የሚያደርገው እንቅስቃሴም የሚመሰገንና በሌሎች የአገሪቱ ግዛቶችም ሊለመድ የሚገባው በጎ ተግባር ነው እያሉ በገዳሙ መንፈሳዊ አገልግሎት ያገኙ በርካታ ምእመናንን ሀሳባቸውን ሲገልጹ ቆይተዋል።

በዚሁ ገዳም አስተባባሪነት የአብነት ትምህርታቸውን ተከታትለው ለአገልግሎት ለተዘጋጁ ተማሪዎች ለሢመተ ዲቁና ከተመረጡበት ቀን ጀምሮ እስከሚሾሙበት ጊዜ ድረስም በኪዳንና በቅዳሴ ጸሎት ላይ ስማቸው እየተጠራ ይጸለይላቸዋል።

ከመሾማቸው አስቀድሞ ለዲያቆናቱ አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ ሥልጠና ይሰጣቸዋል። ሹመቱ ከተፈጸመላቸው በኋላም በምዕመናን ፊት ቃል ይገባሉ።
በ፳፻፲፭ ዓ/ም የደብረ ታቦር በዓል ላይ የተገኙት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከፍ ሲል በተገለጸው መልኩ ሥርዓተ ዲቁና ለመቀበል ለተዘጋጁ አራት ተማሪዎች የዲቁና ማዕረግ ሰጥተዋል። ከዲያቆናቱ መካከልም የቤተክርስቲያንን የአብነት ትምህርት በሚገባ የተማሩና ወደ መዘምርነት የተቃረቡ፣ ቅዳሴ፣ ሰዓታት፣ በሥርዓተ ማኅሌት መሳተፍ እንዲሁም ቅኔ መመራትን የቻሉ ተማሪዎች ይገኙበታል።
ከዚህም በተጨማሪ ሁሉም ዲያቆናት በወጣላቸው መርሐ ግብር መሠረት በእንግሊዝኛ ቋንቋ ይሰብካሉ።

ይህን አገልግሎት የተመለከቱት ብፁዕ (ዶ/ር) አቡነ ጴጥሮስም ገዳሙ ሊጠናከር፣ ሊስፋፋና ተገቢው ድጋፍ ሁሉ ሊደረግለት እንደሚገባ የገለጹ ሲሆን በሰሜን አሜሪካን ተተኪ አገልጋይ መሆን የሚችሉ ዘመኑን የዋጁና ሰይፍ በክልኤ የሆኑ አገልጋዮችን የማፍራቱን
ሂደትም አጠናክሮ እንዲቀጥል አደራ በማለት አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: በቄለም ወለጋ ሀገረ ስብከት መዋቅራዊ አደረጃጀቱን የጠበቀ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ገለጹ። Link to: በቄለም ወለጋ ሀገረ ስብከት መዋቅራዊ አደረጃጀቱን የጠበቀ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ገለጹ። በቄለም ወለጋ ሀገረ ስብከት መዋቅራዊ አደረጃጀቱን... Link to: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን የ፲ ዓመት መሪ እቅድ ሥልጠና በብፁዕ ቅዱስ ፓትርያርኩ ቃለ በረከት ተከፈተ:: Link to: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን የ፲ ዓመት መሪ እቅድ ሥልጠና በብፁዕ ቅዱስ ፓትርያርኩ ቃለ በረከት ተከፈተ:: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top