ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
አገር አቀፍ የስብከተ ወንጌል አልግሎትን ለማጠናከር የሚያስችል የምክክር መድረክ ተካሔደ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ አገር አቀፍ የስብከተ ወንጌልን አገልግሎት በተጠና፣ተቋማዊ በሆነና ለውጥ ሊያመጣ በሚያስችል መልኩ ማከናወን የሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከሚመለከታቸው አካላትና ከስባቱ ክፍላተ ከተማ ሥራ አስኪያጆችና የስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊዎች ጋር ጥር ፲፮ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መሰብሰቢያ አዳራሽ የምክክር መድረክ አካሔደ።
በቦሰት ወረዳ ቤተ ክህነት የመርቆ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ፡መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ባልታወቁ የታጠቁ ኃይሎች ተቃጥሏል፡፡
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በቦሰት ወረዳ ቤተ ክህነት የመርቆ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን በአሳዛኝ ሁኔታ ባልታወቁ የታጠቁ ኃይሎች ትናንት ጥር 17/2016 ዓ.ም አመሻሽ ላይ ተቃጥሏል፡፡
“ችግር እና መከራ ሁሉ ጊዜያዊ ነው፤ በእምነት በመጽናት ችግርን የምናልፍ አስተዋዮች መኾን አለብን”ብፁዕ አቡነ አብርሃም
በየዓመቱ በባሕር ዳር ከተማ በድምቀት የሚከበረው” የቅዱስ ጊዮርጊስ ስባር አጽሙ” ሃይማኖታዊ በዓል ዛሬም በድምቀት እየተከበረ ነው።
የዴንቨር ኮሎራዶና አካባቢው ሀገረ ስብከት ፮ኛው የሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ በመካሔድ ላይ ነው።
በሰሜን አሜሪካ በዴንቨር ከተማ በዛሬው ዕለት የሀገረ ስብከቱ ፮ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ መካሔድ ጀመረ። በ፮ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ የተገኙት የዴንቨር ኮሎራዶና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ጉባኤውን በፀሎት የከፈቱት ሲሆን ጉባኤውንም በርዕሰ መንበርነት እየመሩት ይገኛሉ።
በጋምቤላ ሀገረ ስብከት በጋምቤላ ከተማ ባሕረ ጥምቀት ለአምስት ቀናት ሲካሄድ የሰነበተው የስብከተ ወንጌል ጉባኤ ተጠናቀቀ።
ከበዓለ ጥምቀት ማለትም ከጥር 10 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ሲከናወን የሰነበተው የስብከተ ወንጌልና የመዝሙር አገልግሎት በደመቀ ዝግጅት ተጠናቋል።
የ፳፻፲ወ፮ ዓ.ም ዘመነ ዮሐንስ የጥምቀት በዓል አከባበር በጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት አምስቱም ሀገራት በጀርመን፣ በኔዘርላንድ፣ በስዊዘርላንድ፣ በኦስትሪያ እና በፖላንድ ባሉ ወረዳ አብያተ ክህነትና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በጥምረትና በድምቀት ተከበረ ።
በዓሉ በተለይ በጀርመን ሔሰን ግዛት ፍራንክፈርት ከተማና አካባቢው ያሉ አራት አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በጥምረት በደብረ ኀይል ቅዱስ ዑራኤል ወቅዱስ ያሬድ ቤ/ክ አዘጋጅነት ጥር ፲፪ ቀን የ፳፻፲ወ፮ ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ የጀርመንና አካባቢው እና የምሥራቅ ጎጃም አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በማኅሌት በቅዳሴ ሥርዓተ ጥምቀቱን በመፈጸም በድምቀት ተከብሮ ውሏል ።
በጋምቤላ ሀገረ ስብከት በጋምቤላ ከተማ የመድኃኔ ዓለም እና የአቡነ አረጋዊ ታቦታተ ሕግ ወደመንበረ ክብራቸው በሰላም ገብተዋል።
ጥር 14 ቀን 2016 ዓ.ም
የከተራ፣የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በአላማጣ በድምቀት ተከብሮ ዋለ።
የከተራ፣የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በራያ አላማጣና በስድስቱ ወረዳዎች በታላቅ መንፈሳዊ ሥነሥርዓት ተከብሮ መዋሉን የሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤት በላከልን ዘገባ ገለጸ።ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ተወልደው ባደጉበት ራያ አላማጣ ከተማ ከሦስት ዓመታት በኋላ በዓላቱን እንዳከበሩ የገለጸው የሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤት ሕዝበ ክርስቲያኑ በነቂስ በመውጣት በዓሉም ፍጹም ሰላማዊና ደማቅ በሆነ መልኩ ማክበሩን ገልጿል።
የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የጌታችን፣ የአምላካችን፣ የመድኀኒታችን፣ የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል ሰላማዊ በሆነ መልኩ ተከብሮ እንዲውል ላደረጋችሁ ሁሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምስጋናዋን ታቀርባለች፤
በአጠቃላይ የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የጥምቀት በዓላችን ፍጹም መንፈሳዊና ደማቅ በሆነ መልኩ ተከብሮ እንዲውል ልዩ ልዩ ድጋፍ ያደረጋችሁ አካላትና የተለያዩ ዕምነት ተከታይ ወገኖቻችን ያደረጋችሁትን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ቤተክርስቲያናችን በልዩ አድናቆት የምትመለከተው ከመሆኑም በላይ ከፍተኛ ምስጋናዋን ታቀርባለች።
በዓለ ጥምቀትን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ላይ ብቻ ያተኮረ ምላሽ እንዲሰጥ መመሪያ ተላለፈ።
በዓለ ጥምቀትን አስመልክቶ የሚተላለፉ መልእክቶች የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ላይ ብቻ ያተኮሩ እንዲሆኑ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መመሪያ አስተላልፈዋል።