ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ግንቦት ፳፩ ቀን ፳፱፲ወ፮ ዓ/ም ባደረገው የጠዋቱ የግንቦት ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ ሰባት አበው ሊቃነ ጳጳሳትን በመወያያ አጀንዳ አርቃቂነት ሰየመ።
ግንቦት ፳፩ ቀን ፳፱፲ወ፮ ዓ/ም
“ተደራሽነት ያለው የሕዝብ ግንኙነት ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን” በሚል ርዕስ ለአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል ኃላፊዎች ሲሰጥ የነበረው ሥልጠና ተጠናቀቀ።
የተዘጋጀው በለ ፲ ነጥብ የአቋም መግለጫ ተነቧል። የአቋም መንለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል።
“የአብነት ትምህርት ቤት ለቤተክርስቲያን መሠረት ነው” በሚል መሪ ቃል በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የትምህርትና ማሠልጠኛ መምሪያ ከመላው ኢትዮጵያ ለመጡ የአብነት መምህራን ያዘጋጀው የምክክርና ሥልጠና ጉባኤ ተጠናቀቀ፡፡
ዘጋቢ መ/ር ጌታቸው በቀለ
(© EOTC TV ግንቦት ፲፬ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም አዲስ አበባ)
“ተደራሽነት ያለው የሕዝብ ግንኙነት ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን” በሚል ርዕስ ለአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል ኃላፊዎች እየተሰጠ ያለው ሥልጠና በመካሔድ ላይ ነው ።
ግንቦት ፲፮ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
****
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
የቤተክርስቲያናችን ሕዝብ ግንኙነት ከላይ እስከ ታች ተናቦና ተሳስሮ መሰራት ይኖርበታል።
ግንቦት ፲፭ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
ቅዱስ ፓትርያርኩ በደቡብ አፍሪካ ጁሐንስበርግ ጽርሐ ጽዮንመድኀኔዓለም ካቴድራል የተመሰረተበትን ፳፭ኛ ዓመት በዓል አከበሩ።
ግንቦት ፬ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ/ም
“””””””””””””””””””””””””””
ደቡብ አፍሪካ- ጁሐንስበርግ
“የማይኾን ጸጸት እንዳንጸጸት በሰዓቱ እና በጊዜው ንስሐ እንግባ” ብጹዕ አቡነ አብርሃም ፤
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲን የጠቅላይ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳር እና ሰሜን ጎጃም ሀገረ ሰብክት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ አብርሃም የስቅለት በዓልን ምክንያት በማድረግ ትምህርት እና አባታዊ ምክር ሰጥተዋል፡፡
የ”ገብረ ሰላመ” በዓል ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት በደማቅ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓት ተከበረ።
በየዓመቱ በበዓለ ትንሣኤ ዋዜማ “በቀዳም ስዑር” የሚከበረው የገብረ ሰላመ በዓል ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአከኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በተገኙበት ዛሬ ሚያዝያ ፳፮ ቀን ፳፻፲ወ፮ ዓ/ም በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በደማቅ ሃይማኖታዊ ሥርዓተ አምልኮ ተከበረ።
በኮሪደር ልማት ምክንያት የተነሳው የቤተ ክርስቲያኗ ህንጻ የመልሶ ግንባታ ስራ ተጀመረ
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በኮሪደር ልማት ምክንያት የተነሳውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሕንጻ የመልሶ ግንባታ ስራ አስጀምረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሔደውን የኮሪደር ልማት ተከትሎ በርካታ ሥራዎችን በማከናወን ላይ ትገኛለች።
ከከተማ አስተዳደሩ ከንቲባና ከሥራ ኃላፊዎቹ ጋር የተደረገውን ውይይትና ውጤቱን መሠረት በማድረግም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ የቀረበለትን ሪፖርት መነሻ በማድረግ ውሳኔና ምክረ ሀሳብ ለቋሚ ሲኖዶስ አቅርቧል።