ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
የ፳፻፲ወ፮ ዓ.ም ዘመነ ዮሐንስ የጥምቀት በዓል አከባበር በጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት አምስቱም ሀገራት በጀርመን፣ በኔዘርላንድ፣ በስዊዘርላንድ፣ በኦስትሪያ እና በፖላንድ ባሉ ወረዳ አብያተ ክህነትና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በጥምረትና በድምቀት ተከበረ ።
በዓሉ በተለይ በጀርመን ሔሰን ግዛት ፍራንክፈርት ከተማና አካባቢው ያሉ አራት አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በጥምረት በደብረ ኀይል ቅዱስ ዑራኤል ወቅዱስ ያሬድ ቤ/ክ አዘጋጅነት ጥር ፲፪ ቀን የ፳፻፲ወ፮ ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ የጀርመንና አካባቢው እና የምሥራቅ ጎጃም አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በማኅሌት በቅዳሴ ሥርዓተ ጥምቀቱን በመፈጸም በድምቀት ተከብሮ ውሏል ።
በጋምቤላ ሀገረ ስብከት በጋምቤላ ከተማ የመድኃኔ ዓለም እና የአቡነ አረጋዊ ታቦታተ ሕግ ወደመንበረ ክብራቸው በሰላም ገብተዋል።
ጥር 14 ቀን 2016 ዓ.ም
የከተራ፣የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በአላማጣ በድምቀት ተከብሮ ዋለ።
የከተራ፣የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በራያ አላማጣና በስድስቱ ወረዳዎች በታላቅ መንፈሳዊ ሥነሥርዓት ተከብሮ መዋሉን የሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤት በላከልን ዘገባ ገለጸ።ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ተወልደው ባደጉበት ራያ አላማጣ ከተማ ከሦስት ዓመታት በኋላ በዓላቱን እንዳከበሩ የገለጸው የሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤት ሕዝበ ክርስቲያኑ በነቂስ በመውጣት በዓሉም ፍጹም ሰላማዊና ደማቅ በሆነ መልኩ ማክበሩን ገልጿል።
የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የጌታችን፣ የአምላካችን፣ የመድኀኒታችን፣ የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል ሰላማዊ በሆነ መልኩ ተከብሮ እንዲውል ላደረጋችሁ ሁሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ምስጋናዋን ታቀርባለች፤
በአጠቃላይ የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የጥምቀት በዓላችን ፍጹም መንፈሳዊና ደማቅ በሆነ መልኩ ተከብሮ እንዲውል ልዩ ልዩ ድጋፍ ያደረጋችሁ አካላትና የተለያዩ ዕምነት ተከታይ ወገኖቻችን ያደረጋችሁትን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ቤተክርስቲያናችን በልዩ አድናቆት የምትመለከተው ከመሆኑም በላይ ከፍተኛ ምስጋናዋን ታቀርባለች።
በዓለ ጥምቀትን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ላይ ብቻ ያተኮረ ምላሽ እንዲሰጥ መመሪያ ተላለፈ።
በዓለ ጥምቀትን አስመልክቶ የሚተላለፉ መልእክቶች የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ላይ ብቻ ያተኮሩ እንዲሆኑ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መመሪያ አስተላልፈዋል።
የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የጥምቀት በዓል አከባበር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመጠናቀቅ ላይ ናቸው።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ከሚከበሩ የአደባባይ በዓላት መካከል የጥምቀት በዓል አንዱና ዋነኛው ነው። በዩኔስኮ በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የአደባባይ መንፈሳዊ በዓላችን የጥምቀት በዓል ዘንድሮም በታላቅ ሥነሥርዓት የሚከበር ሲሆን በዓሉ በደመቀና ባማረ መልኩ ተከብሮ መዋል ይችል ዘንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት በብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሰብሳቢነት ዐቢይ ኮሚቴ ተጀራጅቶ በየዘርፉ የተጣለበትን ኃላፊነት በመወጣት ላይ ይገኛል።
ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ በሀገረ ስብከታቸው የሚያደርጉትን ሐዋርያዊ ጉዞ አጠናክረው ቀጥለዋል።
* በዋጃ አካባቢ ደብረ ሣሌም ቦታ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ለሚታነጸው ሕንፃ ቤተክርስቲያን የአንድ መቶ ሺህ ብር ድጋፍ አድርገዋል።
* አዲስ የተሰራውን የአየር ማረፊያ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያንን ቅዳሴ ቤት አክብረዋል፤ሃያ ሺህ ብር የበረከት ልገሳ አድርገዋል።
*በኮረም ከተማ ለሚታነጸው የመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የመሰረት ድንጋይ አኑረዋል።የአንድ መቶ ሺህ ብር ድጋፍም አድርገዋል።
ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል የጥምቀት በዓልን ለማክበር ጋምቤላ ገቡ፤ከአሥር ሚሊየን ብር በላይ ንዋያተ ቅዱሳን ይዘው ተጉዘዋል።
ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል የጋምቤላ ፣ የቄለም ወለጋ፣ የአሶሳ እና የደቡብ ሱዳን አሁጉረ ስቅከት ሊቀ ጳጳስ የጋምቤላ ክልልና የቤንሻንጉል ጉምዝ አሶሳ አህጉረ ስብከት የኃማኖት ተቋማት ሰብሳቢና የልማትና የሰላም አምባሳደር ጥር 4 ቀን 2016 ዓ.ም ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ተነስተው በመኪና ጉዞ በማድረግ ከ10,000,000 ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው ልዩ ልዩ ንዋተ ቅድሳትን በመያዝ ወለጋ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናትን እየባረኩና የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን በማስከፈትና የንዋተ ቅድሳት ድጋፍ በመድረግ ጥር 6 ቀን 2016 ዓ.ም ጋምቤላ ገብተዋል ።
ቅዱስ ፓትርያርኩ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ለሚያስገነባው ባለ ሰባት ወለል ሕንጻ የመሠረት ደንጊያ አስቀመጡ።
በብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሚመራው ፣የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የካህናት ማሰልጠኛ ሆኖ ከዘመናዊ ትምህርት ቤት እስከመንፈሳዊ ኮሌጅና ኃላም ከፍተኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ነገረ መለኮት ወይም ቲዎሎጂ ትምህርት ማስተማሪያ ፣የጥናትና ምርምር ማዕከል ሆኖ ለ60 ዓመታት ያህል መንፈሳዊ አገልግሎት መስጠቱ ይታወቃል።
የደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል በ22 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው የእንጀራ ማምረቻ በቅዱስ ፓትርያርኩ ተመረቀ።
የእንጀራ ማምረቻው በሒደት ከስድስት ሺህ እስከ አስር ሺህ እንጀራ የሚያመርት መሆኑ ተገልጽዋል።