ልማት በቤተ ክርስቲያን
ልዮ ዕትም መጽሔት
ይህ ”ልማት በቤተክርስቲያን“ የተሰኘ ልዮ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
በኦስሎ ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምርህታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ደቀመዛሙርት ማዕርገ ዲቁና ተቀበሉ።
በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ኤልያስ መልካም ፈቃድ አሳሳቢነት የአብነት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ለቆዩት አራት ደቀ መዛሙርት የዲቁና ሥልጣነ ክህነት በሰጡበት ወቅት ለአገልጋዮቹ በሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ትምህርት አስተምረው በዓለም ዙሪያ ያለችውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን በቅንነትና በእውቀት እንዲያገለግሏትም አባታዊ መመሪያም አስተላልፈዋል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ የካቲት 11/06/2016 ዓ/ም ለሰባት ማኅበራት የዕውቅና ሰርተ ፍኬት ሰጠ።
የተሰጣቸው ሰርተፍኬት ለሦስት ተከታታይ ዓመታት ይቆያል ተብሏል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የማኅበረ ቅዱሳን አመራሮችን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።
የካቲት ፭ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር እና ሰሜን ጎጃም አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰዋሰወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሥራ ጉብኝት አደረጉ።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር እና ሰሜን ጎጃም አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰዋሰወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ አስተዳደር እና ደቀመዛሙርትን በመጎብኘት አባታዊ ቡራኬ እና የሥራ መመሪያን አስተላልፈዋል፡፡
የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻና ግብረ ሰዶማዊነትን አስመልከቶ እየተደረጉ ያሉ ሁለገብ ተጽእኖዎችንና መመሪያ የማስለወጥ ማግባባቶችን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡
የካቲት ፬ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በትላንትናው እለት የብፁዕ አቡነ ፋኖኤል የዋሽንግተን ዲሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወላጅ እናት የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ተከኝተው አሸኛኘት አደረጉላቸው።
የካቲት ፬ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ዓመታዊ የሥልጠናና የውይይት መርሐ ግብሩን ጀመረ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ በየዓመቱ የሚያካሂደውንና ወዘቅታዊና ዘላቂ የቤተክርስቲያናችን ጉዳይ ላይ በየዓመቱ የሚያደርገውን የሁለት ቀናት የሥልጠናና የውይይት መርሐ ግብር ዛሬ ጥር ፴ ቀን ፳፻፲ወ፮ ዓ/ም ጀመረ።
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ አገር እንዳይገቡ ተከለከሉ።
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአሜሪካ የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎት ጨርሰው ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ እንዳይገቡ መከልከላቸው ተሰምቷል።
የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት እና የውጭ ግንኙነት መምሪያ ሓላፊዎች ከእስራኤል አምባሳደር ጋር ተወያዩ።
የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጸሐፊ ክቡር መልአከ ሕይወት ቆሞስ አባ ኃይለገብርኤል ነጋሽ እና የውጭ ግንኙነት መምሪያ ሓላፊ ሊቀ ካህናት ደረጀ መንግሥቱ በኢትዮጵያ ከእስራኤል አምባሳደር ክቡር አለልኝ አድማሱ እና የኤምባሲው ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ተወያይተዋል ።
ማኅበረ ቅዱሳን በዳውሮ ሀገረ ስብከት አዳሪ የአብነት ት/ቤት አስመረቀ።
በማኅበረ ቅዱሳን አስተባባሪነት በዳውሮ ሀ/ስብከት በምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም የተገነባው አዳሪ የአብነት ት/ቤት ጥር 23 ቀን 2016 ዓ.ም የዳውሮና ኮንታ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ፣ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የአካባቢው ምእመናን በተገኙበት ተመርቋል።