ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመስቀል አደባባይ የሚከበረውን የደመራ በዓልን አስመልክቶ መልእክት አስተላለፉ።

ብፁዕነታቸው በመግቢያቸው ስለ ትግስት አስፈላጊነት እና ጠቀሜታ ትምህርት የሰጡ ሲሆን በበዓሉ ላይ የሚፈትኑ ጉዳዮች ሊገጥሙን ስለሚችሉ በትዕግስት ማለፍ አለብን ብለዋለል። በማስከተልም የዕለቱን መርሐ ግብር ያስተዋወቁ ሲሆን በይበልጥም ሰዓትን ማክበር ከፍተኛ ትኩረት እንደሚሰጠው አሳስበዋል። ብፁዕነታቸው የመግቢያ ባጅ እደላው በሕግና በሥርዓት ትኩረት ተሰጥቶት የሚከናወን መሆኑን ገልጸዋል።

በመቅደላ ጦርነት ወቅት በእንግሊዝ ወታደሮች ከተዘረፉ የብራና መጻሕፍትና ልዩ ልዩ ንዋየ ቅድሳት መካከል እንደሆነ የሚገመት አንድ ጽላት እና የተለያዩ ቅርሶች በበጐ አድራጊዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ የርክክብ ሥነ ሥርዓት በታላቋ ብሪታንያ ለንደን ከተማ ተከናወነ።

በዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ለንደን (UCL) መምህር የሆኑትና ለረጅም ጊዜ በኢትዮጵያና በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤክርስቲያን ጉዳይ ላይ ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር ጃኮፖ ግኒስኪ በመቅደላ ጦርነት ዘመን ከአገር እንደወጣ የሚገመትና በእርሳቸው እጅ የነበረ ጽላት ወደ ሀገሩና ወደ መንበረ ክብሩ እንዲመለስ ከፍተኛውን አስተዋጽዖ እንዳበረከቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን በመወከል ጽላቱን የተረከቡት የልዑካን ቡድኑ ተወካይ ቀሲስ ዶ/ር አባተ ጐበና ምስጋናቸውን በልዑካኑ ስም ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።

ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል በዶምቢዶሎ ሎና በቄለም ወለጋ ልዩልዩ የልማት ሥራዎችን አከናወኑ ለችግረኛ ተማሪዎችም የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አየረጉ።

ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል የጋምቤላ፣የአስሳ፣የቄለም ወለጋና የደቡብ ሱዳን አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በደምቢዶሎ ከተማ በሚያደርጉት ሐዋርያዊ አገልግሎት በደምቢዶሎ ከተማ ቀበሌ03 በአርባ ቀናት ተሰርቶ የተጠናቀቀውን የቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን መስከረም 6ቀን 2016ዓ.ም ቅዳሴ ቤቱን ማክበራቸውን የሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤት ሕዝብ ግንኙነት ክፍል በላከልን ዘገባ ገልጿል።

የጥቅምት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ጥሪ ተላለፈ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዓመት ሁለት ጊዜ ከሚያደርጋቸው የምልአተ ጉባኤ ስብሰባዎች አንዱ የሆነው የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ መሆኑ ይታወቃል። የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የዘንድሮው የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ ከጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፲፮ ዓ/ም ጀምሮ እንደሚካሄድ በመግለጽ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና ጳጳሳት ጥቅምት ፲፩ ቀን ፳፻፲፮ ዓ/ም በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ እንዲገኙ መንፈሳዊ ጥሪውን አስተላልፏል።

በውጭ አገር ለምትገኙ አህጉረ ስብከት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተላለፈ መልዕክት

ለሁለተኛ ጊዜ በውጭ አገር ለሚገኙ አህጉረ ስብከት ጥሪ ተላልፏል።ስለሆነም በተላለፈው ጥሪ መሰረት ዝርዝራችሁ ከዚህ ደብዳቤ ጋር የተለጠፈው አህጉረ ስብከት በአስቸኳይ ሪፖርታችሁን እንድታቀርቡና በገጉባኤው ላይ እንድትሳተፉ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን ።

የመስቀል ደመራ በዓል የቅድመ ዝግጅት ሥራ በአምስት ማዕከላት በመከናወን ላይ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል የቅድመ ዝግጅት ሥራውን እያከናወነ ነው።

በዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የደረሰውን ዝርፊያ በተመለከተ አሰፈላጊው ክትትል እየተደረገ ነው።

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሚገኘው የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም በትላንትናው እለት ማንነታቸው ባልታወቁ ዘራፊዎች የደረሰበትን ዝርፊያ በተመለከተ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስፈላጊውን ክትትልና ማጣራት በማድረግ ላይ የምትገኝ ሲሆን በጉዳዩ ዙሪያም ከሚመለከታቸው የመንግሥት የጸጥታ አካላት ጋር እየተነጋገረችበት ነው።

የቅድስት ልደታ ጤና ኮሌጅ በተከታታይ ዓመታት ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ።

የቅድስት ልደታ ጤና ኮሌጅ በተከታታይ ዓመታት ያስተማራቸውን ተማሪዎች ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ በተገኙበት አስመረቀ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የ፳፻ ፲ወ፮ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል አከባበር የዝግጅት ሥራ ግምገማ ተካሔደ ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በ፳፻፲፭ ዓ/ም የሥራ ዓመት በነበረው የሥራና የአገልግሎት አፈጻጸም ዙሪያ አጠቃላይ የጠቅላይ ጽ/ቤቱ ሠራተኞች በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አሥኪያጁ በብፁዕ አቡነ አብርሃም መሪነት በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ሠፊ ውይይት አደረጉ።

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤ ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዓውደ ዓመት ዘዕስራ ምእት ዐሠርቱ ወስድስቱ ዓመተ ምሕረት

አዲሱ ዓመት የሰላምና የፍቅር፣ የዕርቅና የይቅርታ የተፈናቀለው ወደቀየው የሚመለስበት፣ ሆድ የባሰው የሚጽናናበት፣ ፍትሕና ርትዕ የሚሰፍንበት የመሳሪያ ድምፅ የማይሰማበት ፍጹም የተግባቦት ዓመት እንዲሆንልን እየጸለይን ሁሉም ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን ለዚህ ቅዱስ ጥሪ አዎንታዊ መልስ እንድትሰጡ አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም በድጋሚ እናስተላልፋለን፡፡

በፌስቡክ ያግኙን

የኅትመትና ሚዲያ ዋና ክፍል

ብፁዕ አቡነ አብርሃም

የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ

በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ

ለውስጥ አገልግሎት

የኢሜይል አገልግሎት

ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን

ርእይ

ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት

ተልእኮ

  • የእግዚአብሔርን ቃል ለሰው ልጆች ሁሉ ማስተማርና ማዳረስ

  • ሰውን በሁለንተናዊ ሰብእናው ማገልገልና ማዳን

  • ሰውን ሁሉ በነገረ መለኮትና በነገረ ጥበብ ትምህርት በማልማት በመንፈሳዊም ሆነ በሥጋዊ ሕይወቱ የተሻለ ኑሮ እንዲኖረው ማድረግ

  • ጥራትና ብቃት፣ ፍትሐዊነትና እኩል ተደራሽነት ያለው መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ለሰው ሁሉ ማበርከት

  • የተለያዩ የልማት መርሀ ግብሮችን በመንደፍ ቤተ ክርስቲያንን በኢኮኖሚ ማበልጸግ

  • በቴክኖሎጂ ስልት የሚመራና አዋጭነቱ አስተማማኝ የሆነ የጠቅላላ ሀብት አስተዳደርና አጠቃቀም እንዲረጋገጥ ማድረግ

  • የሰው ልጆች ሁሉ እኩልነት፣ ሰላምና ፍትሕ፣ ፍቅርና ስምምነት እንዲጠበቅ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ

  • የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አሰራር ግልጽ፣ ለሁሉም ተደራሽና ችግር ፈቺ እንዲሆን ማድረግ

ዕሴቶች

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅሊናን የሚረታ፣ አእምሮን የሚመሥጥ፣ ከጥንተ ፍጥረት ተነሥቶ በዘመነ አበው በሕገ ልቡና፣ በዘመነ ብሉይ በሕግ ኦሪት፣ ተራምዶ መዳረሻውን ሕገ ወንጌል ያደረገ ጥንታዊ ክርስቶሳዊና ሐዋርያዊ ትምህርተ ሃይማኖት፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን፣ በያሬዳዊ ጣዕመ ዜማ የታጀበ ሥርዐተ አምልኮ፣ በጽሑፍና በትውልድ ቅብብሎሽ የተወረሰ የረጅም ጊዜ ትውፊት ባህልና ታሪክ

  • በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የበለጸገ፣ እግዚአብሔርን የሚወድና የሚፈራ ለእግዚአብሔር የሚታዘዝና ምክረ ካህን የሚቀበል ከስልሳ ሚልዮን በላይ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ

  • ለምጣኔ ሃብት ዕድገት እጅግ የምትጠቅም በውብ ሥነ ተፈጥሮና በሥነ ጽሑፍ፣ በሥነ ጥበብና በኪነ ጥበብ፣ በታሪክና በቅርስ ሃብት የበለጸገች እንዲሁም በሃይማኖት፣ በነጻነትና በአንድነት የደመቀች ሃገር

  • የእግዚአብሔርን ቃል ከሃገር ውስጥ ባሻገር ለመላው ዓለም ማዳረስ የሚችሉ ከግማሽ ሚልዮን ያላነሱ ሊቃውንት፣ ቀሳውስት፣ ዲያቆናት፣ ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ከሁለት ሺሕ ያላነሱ ገዳማት

  • መላውን ዓለም እያዳረሰና እየሰፋ የሚገኝ ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ የተዋቀረ ጠንካራ መዋቅር ያላት መሆኗ

ያግኙን

+251 111 55 0098 P.O.Box 1283 A.A. 5 KILLO, ADDIS ABABA, ETHIOPIA በፌስቡክ ያግኙን የዩትዩብ ቻነል