ልማት በቤተ ክርስቲያን

ልዮ ዕትም መጽሔት

ይህ ”ልማት በቤተክርስቲያን“ የተሰኘ ልዮ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።

ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች

የመርካቶ ደብረ አሚን ዳግሚት ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ሕንጻ ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ቤት ተከበረ።

በትናንትናው ዕለት የእድሳት ሥራው ተጠናቆ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ተባርኮ መንፈሳዊ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ታለቁ ገዳም በዛሬው ዕለት ብፁዕ አቡነ ቶማስ የአዊ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ታቦተ አቡነ ተክለሃይማኖት ዑደት በማድረግ በዓሉን ለማክበር የተሰበሰቡ ውሉደ ክህነትና ውሉደ ጥምቀትን በመባረክ በዓሉ ተከብሯል።

የመርካቶ ደብረ አሚን ዳግሚት ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ሕንጻ ቤተክርስቲያን እድሳት ተጠናቆ በብፁዕ ወቅዱስ አባታችን ተባርኮለአገልግሎት መስጠት ጀመረ።

በ፲፰፻፺ወ፰ ዓ/ም በንጉሠ ነገሥት አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት የተመሠረተውና ፻፲፰ ዓመታት ያስቆጠረው ሕንጻ ቤተመቅደስ በእድሜ ርዝመት ምክንያት በመጎዳቱ ምክንያት ለመንፈሳዊ አገልግሎት አመቺ በሆነ መንገድ እድሳት ተደርጎለት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ተባርኮ መንፈሳዊ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

አገር አቀፍ የስብከተ ወንጌል አልግሎትን ለማጠናከር የሚያስችል የምክክር መድረክ ተካሔደ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ አገር አቀፍ የስብከተ ወንጌልን አገልግሎት በተጠና፣ተቋማዊ በሆነና ለውጥ ሊያመጣ በሚያስችል መልኩ ማከናወን የሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከሚመለከታቸው አካላትና ከስባቱ ክፍላተ ከተማ ሥራ አስኪያጆችና የስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊዎች ጋር ጥር ፲፮ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መሰብሰቢያ አዳራሽ የምክክር መድረክ አካሔደ።

በቦሰት ወረዳ ቤተ ክህነት የመርቆ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ፡መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ባልታወቁ የታጠቁ ኃይሎች ተቃጥሏል፡፡

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በቦሰት ወረዳ ቤተ ክህነት የመርቆ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን በአሳዛኝ ሁኔታ ባልታወቁ የታጠቁ ኃይሎች ትናንት ጥር 17/2016 ዓ.ም አመሻሽ ላይ ተቃጥሏል፡፡

“ችግር እና መከራ ሁሉ ጊዜያዊ ነው፤ በእምነት በመጽናት ችግርን የምናልፍ አስተዋዮች መኾን አለብን”ብፁዕ አቡነ አብርሃም

በየዓመቱ በባሕር ዳር ከተማ በድምቀት የሚከበረው” የቅዱስ ጊዮርጊስ ስባር አጽሙ” ሃይማኖታዊ በዓል ዛሬም በድምቀት እየተከበረ ነው።

የዴንቨር ኮሎራዶና አካባቢው ሀገረ ስብከት ፮ኛው የሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ በመካሔድ ላይ ነው።

በሰሜን አሜሪካ በዴንቨር ከተማ በዛሬው ዕለት የሀገረ ስብከቱ ፮ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ መካሔድ ጀመረ። በ፮ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ የተገኙት የዴንቨር ኮሎራዶና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ጉባኤውን በፀሎት የከፈቱት ሲሆን ጉባኤውንም በርዕሰ መንበርነት እየመሩት ይገኛሉ።

በጋምቤላ ሀገረ ስብከት በጋምቤላ ከተማ ባሕረ ጥምቀት ለአምስት ቀናት ሲካሄድ የሰነበተው የስብከተ ወንጌል ጉባኤ ተጠናቀቀ።

ከበዓለ ጥምቀት ማለትም ከጥር 10 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ሲከናወን የሰነበተው የስብከተ ወንጌልና የመዝሙር አገልግሎት በደመቀ ዝግጅት ተጠናቋል።

የ፳፻፲ወ፮ ዓ.ም ዘመነ ዮሐንስ የጥምቀት በዓል አከባበር በጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት አምስቱም ሀገራት በጀርመን፣ በኔዘርላንድ፣ በስዊዘርላንድ፣ በኦስትሪያ እና በፖላንድ ባሉ ወረዳ አብያተ ክህነትና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በጥምረትና በድምቀት ተከበረ ።

በዓሉ በተለይ በጀርመን ሔሰን ግዛት ፍራንክፈርት ከተማና አካባቢው ያሉ አራት አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት በጥምረት በደብረ ኀይል ቅዱስ ዑራኤል ወቅዱስ ያሬድ ቤ/ክ አዘጋጅነት ጥር ፲፪ ቀን የ፳፻፲ወ፮ ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ የጀርመንና አካባቢው እና የምሥራቅ ጎጃም አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በማኅሌት በቅዳሴ ሥርዓተ ጥምቀቱን በመፈጸም በድምቀት ተከብሮ ውሏል ።

በጋምቤላ ሀገረ ስብከት በጋምቤላ ከተማ የመድኃኔ ዓለም እና የአቡነ አረጋዊ ታቦታተ ሕግ ወደመንበረ ክብራቸው በሰላም ገብተዋል።

ጥር 14 ቀን 2016 ዓ.ም

የከተራ፣የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በአላማጣ በድምቀት ተከብሮ ዋለ።

የከተራ፣የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በራያ አላማጣና በስድስቱ ወረዳዎች በታላቅ መንፈሳዊ ሥነሥርዓት ተከብሮ መዋሉን የሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤት በላከልን ዘገባ ገለጸ።ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ተወልደው ባደጉበት ራያ አላማጣ ከተማ ከሦስት ዓመታት በኋላ በዓላቱን እንዳከበሩ የገለጸው የሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤት ሕዝበ ክርስቲያኑ በነቂስ በመውጣት በዓሉም ፍጹም ሰላማዊና ደማቅ በሆነ መልኩ ማክበሩን ገልጿል።

በፌስቡክ ያግኙን

የኅትመትና ሚዲያ ዋና ክፍል

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ

የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ

የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ልማት በቤተ ክርስቲያን

ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።

ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን

ርእይ

ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት

ተልእኮ

  • የእግዚአብሔርን ቃል ለሰው ልጆች ሁሉ ማስተማርና ማዳረስ

  • ሰውን በሁለንተናዊ ሰብእናው ማገልገልና ማዳን

  • ሰውን ሁሉ በነገረ መለኮትና በነገረ ጥበብ ትምህርት በማልማት በመንፈሳዊም ሆነ በሥጋዊ ሕይወቱ የተሻለ ኑሮ እንዲኖረው ማድረግ

  • ጥራትና ብቃት፣ ፍትሐዊነትና እኩል ተደራሽነት ያለው መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ለሰው ሁሉ ማበርከት

  • የተለያዩ የልማት መርሀ ግብሮችን በመንደፍ ቤተ ክርስቲያንን በኢኮኖሚ ማበልጸግ

  • በቴክኖሎጂ ስልት የሚመራና አዋጭነቱ አስተማማኝ የሆነ የጠቅላላ ሀብት አስተዳደርና አጠቃቀም እንዲረጋገጥ ማድረግ

  • የሰው ልጆች ሁሉ እኩልነት፣ ሰላምና ፍትሕ፣ ፍቅርና ስምምነት እንዲጠበቅ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ

  • የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አሰራር ግልጽ፣ ለሁሉም ተደራሽና ችግር ፈቺ እንዲሆን ማድረግ

ዕሴቶች

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅሊናን የሚረታ፣ አእምሮን የሚመሥጥ፣ ከጥንተ ፍጥረት ተነሥቶ በዘመነ አበው በሕገ ልቡና፣ በዘመነ ብሉይ በሕግ ኦሪት፣ ተራምዶ መዳረሻውን ሕገ ወንጌል ያደረገ ጥንታዊ ክርስቶሳዊና ሐዋርያዊ ትምህርተ ሃይማኖት፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን፣ በያሬዳዊ ጣዕመ ዜማ የታጀበ ሥርዐተ አምልኮ፣ በጽሑፍና በትውልድ ቅብብሎሽ የተወረሰ የረጅም ጊዜ ትውፊት ባህልና ታሪክ

  • በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የበለጸገ፣ እግዚአብሔርን የሚወድና የሚፈራ ለእግዚአብሔር የሚታዘዝና ምክረ ካህን የሚቀበል ከስልሳ ሚልዮን በላይ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ

  • ለምጣኔ ሃብት ዕድገት እጅግ የምትጠቅም በውብ ሥነ ተፈጥሮና በሥነ ጽሑፍ፣ በሥነ ጥበብና በኪነ ጥበብ፣ በታሪክና በቅርስ ሃብት የበለጸገች እንዲሁም በሃይማኖት፣ በነጻነትና በአንድነት የደመቀች ሃገር

  • የእግዚአብሔርን ቃል ከሃገር ውስጥ ባሻገር ለመላው ዓለም ማዳረስ የሚችሉ ከግማሽ ሚልዮን ያላነሱ ሊቃውንት፣ ቀሳውስት፣ ዲያቆናት፣ ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ከሁለት ሺሕ ያላነሱ ገዳማት

  • መላውን ዓለም እያዳረሰና እየሰፋ የሚገኝ ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ የተዋቀረ ጠንካራ መዋቅር ያላት መሆኗ

ያግኙን

+251 111 55 0098 P.O.Box 1283 A.A. 5 KILLO, ADDIS ABABA, ETHIOPIA በፌስቡክ ያግኙን የዩትዩብ ቻነል የቴሌግራም ቻነል