ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ በሀገረ ስብከታቸው የሚያደርጉትን ሐዋርያዊ ጉዞ አጠናክረው ቀጥለዋል።
* በዋጃ አካባቢ ደብረ ሣሌም ቦታ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ለሚታነጸው ሕንፃ ቤተክርስቲያን የአንድ መቶ ሺህ ብር ድጋፍ አድርገዋል።
* አዲስ የተሰራውን የአየር ማረፊያ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያንን ቅዳሴ ቤት አክብረዋል፤ሃያ ሺህ ብር የበረከት ልገሳ አድርገዋል።
*በኮረም ከተማ ለሚታነጸው የመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የመሰረት ድንጋይ አኑረዋል።የአንድ መቶ ሺህ ብር ድጋፍም አድርገዋል።
ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል የጥምቀት በዓልን ለማክበር ጋምቤላ ገቡ፤ከአሥር ሚሊየን ብር በላይ ንዋያተ ቅዱሳን ይዘው ተጉዘዋል።
ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል የጋምቤላ ፣ የቄለም ወለጋ፣ የአሶሳ እና የደቡብ ሱዳን አሁጉረ ስቅከት ሊቀ ጳጳስ የጋምቤላ ክልልና የቤንሻንጉል ጉምዝ አሶሳ አህጉረ ስብከት የኃማኖት ተቋማት ሰብሳቢና የልማትና የሰላም አምባሳደር ጥር 4 ቀን 2016 ዓ.ም ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ተነስተው በመኪና ጉዞ በማድረግ ከ10,000,000 ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው ልዩ ልዩ ንዋተ ቅድሳትን በመያዝ ወለጋ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናትን እየባረኩና የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን በማስከፈትና የንዋተ ቅድሳት ድጋፍ በመድረግ ጥር 6 ቀን 2016 ዓ.ም ጋምቤላ ገብተዋል ።
ቅዱስ ፓትርያርኩ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ለሚያስገነባው ባለ ሰባት ወለል ሕንጻ የመሠረት ደንጊያ አስቀመጡ።
በብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሚመራው ፣የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የካህናት ማሰልጠኛ ሆኖ ከዘመናዊ ትምህርት ቤት እስከመንፈሳዊ ኮሌጅና ኃላም ከፍተኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ነገረ መለኮት ወይም ቲዎሎጂ ትምህርት ማስተማሪያ ፣የጥናትና ምርምር ማዕከል ሆኖ ለ60 ዓመታት ያህል መንፈሳዊ አገልግሎት መስጠቱ ይታወቃል።
የደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያምና ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ካቴድራል በ22 ሚሊዮን ብር ወጪ ያስገነባው የእንጀራ ማምረቻ በቅዱስ ፓትርያርኩ ተመረቀ።
የእንጀራ ማምረቻው በሒደት ከስድስት ሺህ እስከ አስር ሺህ እንጀራ የሚያመርት መሆኑ ተገልጽዋል።
ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡብ እና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይ፣ የቤተ መጻሕፍት ወመዘክርና የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ አላማጣ ከተማ ሲገቡ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው።
ከሦስት ዓመታት በፊት የቋሚ ሲኖዶስ ተረኛ መሆናቸውን ተከትሎ ወደ ጠቅላይ ቤተክህነት የመጡት ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ በሰሜኑ የአገራችን ክፍል በተቀሰቀሰው ጦርነት ምክንያት በአዲስ አበባ ለመቆየት በመገደዳቸው ወደ ሀገረ ስብከታቸው ሳይሔዱ መቆየታቸው ይታወሳል።
የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የጥምቀት በዓል ጥንታዊ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ ሁኔታ ሰላማዊና ደማቅ በሆነ መልኩ እንዲከበር ሁሉም ወገን በኃላፊነት መንፈስ እንዲሠራ ብፁዕ አቡነ አብርሃም አሳሰቡ።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም የጌታችን የአምላካችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓልን በማስመልከት “ከክፉ ሽሽ መልካምንም አድርግ ሰላምን እሻ ተከተላትም” (መዝሙር ፴፬፥፲፫) የሚለውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ኀይለ ቃል መነሻ በማድረግ ባስተላለፉት መልዕክት የጥምቀት በዓል ጥንታዊና ሃይማኖታዊ መሰረቱን በጠበቀ መልኩ ሰላማዊ በሆነና በደማቅ ሥነ ሥርዓት ተከብሮ መዋል ይችል ዘንድ ሕዝበ ክርስቲያኑ በኃላፊነት መንፈስ ሊንቀሳቀስ እንደሚገባው ገልጸዋል።
የብፁእ አቡነ ጴጥሮስ ሐዋርያዊ ጉዞ በቤተ ክርስቲያን ሕግ እና ሥርዓት መሠረት የተፈቀደ ነው።
ብፁእ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኔዮርክ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወደ ሀገረ ስብከታቸው የጥምቀትን በዓል ለማክበር መጓዛቸው ይታወቃል። ጉዟቸውን በተመለከተ በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየተናፈሰ ያለው ወሬ እጅግ የተሳሳተ ሲሆን የብፁእነታቸው ሐዋርያዊ ጉዞ በቤተ ክርስቲያን ሕግ እና ሥርዓት መሠረት በቋሚ ሲኖዶስ የተወሰነ እና በቅዱስ ፓትርያርኩ የተፈቀደ መሆኑን የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አስታውቋል።
የ2016 ዓ.ም የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት የቅዱስ ፓትርያርኩ የእንኳን አደረስዎ መርሐ ግብር በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ተከናወነ።
ታኅሣሥ ፳፱ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም ፣ አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
የሰላማችን ሰንደቅ ዓላማ የሆነው ወልድ ወይም ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ለኛ ተወለደልን
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ዘተናገረ በበዓለ ልደቱ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዐሠርቱ ወስድስቱ ዓመተ ምሕረት፡፡
የቤተክርስቲያናችን የሕግ ባለሙያዎች ኮሚቴ አባል ጠበቃ እና የሕግ አማካሪ አያሌው ቢታኔ ታሠሩ ።
ጠበቃ እና የህግ አማካሪ አያሌው ቢታኔ የዕለት ችሎት ተከራርክሮ ከፍርድ ቤት ወጥቶ ከባለቤቱ እና ከእህቱ ጋር ሜክሲኮ በሚገኘው ነዳጅ ማደያ ለመኪናው ነዳጅ በመቅዳት ላይ ሳለ ሲከታተሉት በነበሩ በመንግስት የጸጥታ አካላት ተወስዶ የታሠረ መሆኑ ታወቀ።