ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች

በቦረና በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ የማሰባሰብ እንቅስቃሴውን የሚያስተባብሩ በብፁዓን አባቶች የሚመራ አምስት አባላት ያሉት ዐቢይ ኮሚቴ ተመደበ፤

. . . በሦስት ብፁዓን አባቶች እና በሁለት የጠቅላይ ቤተክህነት የሥራ ኃላፊዎች የሚመራ ዐቢይ ኮሚቴ እንዲዋቀርና ወደ ሥራ እንዲገባ ያስተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ውሳኔውን እንዲያስፈጽም ኃላፊነት ሰጥቷል።

የጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጉባኤ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/መገናኛ ብዙሃን ሥርጭት ድርጅትና የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በሰው ሃይል እንዲጠናከሩ ወሰነ።

. . . በቀጣይ ጊዜ በሁለቱ ተቋማት በጥምረትና በተናጠል መሰራት ያለባቸው ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎችን ጉባኤው ያመላከተ ሲሆን በተለይም መረጃዎችን የማሰባሰብ፣ወቅታዊ ምላሽ የመስጠትና በየዕለቱ የዜና ሽፋን የመስጠት ጉዳይ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራ አቅጣጫ አስቀምጧል።

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፬ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፩ኛ ዓመት መታሰቢያ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከናወነ።

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ፬ኛ ዓመታ መታሰቢያ በመንበረ ጸባዖት ቅድስ ስላሴ ካቴድራል ብፁዕአን ሊቃነ ጳጳሳት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የሥራ ኃላፊዎች፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ሊቃውተ ቤተክርስቲያን ወዳጆቻቸው እና የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል።

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ፲ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ።

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፲ኛ ዓመት በዓሉ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በታላቅ ሥነሥርዓት ተከብሮ ውሏል።በበዓሉ ላይ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ቴጉሃን ታጋይ ታደለ የጠቅላይ ቤተክህነት የመምሪያና የድርጅትኃላፊዎች፣የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ተገኝተዋል።

የቅዱስነታቸውን ፲ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በማስመልከት የተዘጋጀው “ዜና መዋዕል ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክና ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ መጻህፍት በዛሬው ዕለት ተመረቀ።

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖትን ፲ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በማስመልከት በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት በተቋቋመው የሥነ ጽሑፍ ዝግጅት ኮሚቴ ተዘጋጅቶና በሊቃውንት ጉባኤ ተመርምሮ የተዘጋጀውና ለህትመት የበቃው ዜና መዋዕል ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ መጽሐፍና የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ቃለ በረከት መጽሐፍ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ሚኒስትሮች ፣አምባሳደሮች፣የጠቅላይ ቤተክህነት የመምሪያና የድርጅት ኃላፊዎች፣የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ኃላፊዎች፣የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፣የወጣት ማኅበራት ተወካዮችና የክብር እንግዶች በተገኙበት ዛሬ የካቲት ፳፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ተመርቋል።

ቅዱስነታቸው በብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የሽኝት መርሐ ግብር ላይ ለመገኘት ዛሬ ማለዳ መቐለ ገብተዋል።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት መቐለ አሉላ ኣባነጋ አለም አቀፍ አየር ማረፍያ በሰላም ገብተዋል ።

የብፁዕ አቡነ ዮሐንስ የሕይወት ታሪክ

ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ ትሕትናን፣ አፍቅሮ ቢጽን፣ አክብሮ ሰብእን ዓላማ አድርገው የሚኖሩ በካህናት፣ በምእመናንና በተማሪዎቻቸው ዘንድ ተወዳጅነት ያላቸው፣ በአባትነታቸው ብዙ ፍቅርን ያተረፉ በአጠቃላይ በአርአያነታቸውና በገብረ ገብነታቸው በሁሉም ዘንድ ክብር ያገኙ ደግ አባት ናቸው፡፡

“አባ ” ንዋየ ሥላሴ የተባሉት በፈቃዳቸው ይቅርታ ጠየቁ እንጂ “ያፈነም” “ያስገደደም” አካል የለም ይህ የሐሰት ወሬ ነው ከዚህ ይልቅ በሕገወጥ መንገድ ያላችሁ አካላት በይቅርታ ወደ ቤታችሁ መመለሱ ይበጃል”

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አቀራራቢ ዐቢይ ኮሚቴ

በኢ/ኦ/ተ/ ቤተክርስቲያን በወቅታዊ ችግር ምክንያት የተደራጀው የሽምግልና ኮሚቴ እስከ አሁን የሰራቸውን ስራዎች ለዐቢይ ኮሚቴው ሪፖርት አደረጉ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ በተከሰተው የቀኖና፣የሃይማኖትና የአስተዳደር ጥሰትን ተከትሎ የተፈጠረውን ወቅታዊ ችግር ምክንያት ጉዳዩን በሽምግልና ለመፍታት የተደራጁት የሽምግልና ኮሚቴዎች (የሀገር ሽማግሌዎች) ችግሩ ከተፈጠረ ወዲህ በኮሚቴው የተሠሩ ሥራዎችን እና ወደፊት ሊሠሩ ስለሚገባቸው ጉዳዩች ለዐቢይ ኮሚቴ፣ለብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ለመንበረ ፓትርያርክ እና ለቅዱስ ሲኖዶስጽሕፈት ቤትዛሬ የካቲት ፲፰ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ዓ.ም ሪፖርቱን አቅርቧል።

ቤተክርስቲያን ያወጀችውን አዋጅ ተከትሎ ሃይማኖታዊ ተልእኳቸውን በመፈጸማቸው ከሥራ የተባረሩ፣የታሰሩና የተንገላቱ ኦርቶዶክሳዊያን ሪፖርት እንዲያደርጉ የተላለፈ ጥሪ፤

የካቲት ፲፰ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም

በፌስቡክ ያግኙን

የኅትመትና ሚዲያ ዋና ክፍል

ብፁዕ አቡነ አብርሃም

የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ

በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ

ለውስጥ አገልግሎት

የኢሜይል አገልግሎት

ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን

ርእይ

ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት

ተልእኮ

  • የእግዚአብሔርን ቃል ለሰው ልጆች ሁሉ ማስተማርና ማዳረስ

  • ሰውን በሁለንተናዊ ሰብእናው ማገልገልና ማዳን

  • ሰውን ሁሉ በነገረ መለኮትና በነገረ ጥበብ ትምህርት በማልማት በመንፈሳዊም ሆነ በሥጋዊ ሕይወቱ የተሻለ ኑሮ እንዲኖረው ማድረግ

  • ጥራትና ብቃት፣ ፍትሐዊነትና እኩል ተደራሽነት ያለው መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ለሰው ሁሉ ማበርከት

  • የተለያዩ የልማት መርሀ ግብሮችን በመንደፍ ቤተ ክርስቲያንን በኢኮኖሚ ማበልጸግ

  • በቴክኖሎጂ ስልት የሚመራና አዋጭነቱ አስተማማኝ የሆነ የጠቅላላ ሀብት አስተዳደርና አጠቃቀም እንዲረጋገጥ ማድረግ

  • የሰው ልጆች ሁሉ እኩልነት፣ ሰላምና ፍትሕ፣ ፍቅርና ስምምነት እንዲጠበቅ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ

  • የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አሰራር ግልጽ፣ ለሁሉም ተደራሽና ችግር ፈቺ እንዲሆን ማድረግ

ዕሴቶች

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅሊናን የሚረታ፣ አእምሮን የሚመሥጥ፣ ከጥንተ ፍጥረት ተነሥቶ በዘመነ አበው በሕገ ልቡና፣ በዘመነ ብሉይ በሕግ ኦሪት፣ ተራምዶ መዳረሻውን ሕገ ወንጌል ያደረገ ጥንታዊ ክርስቶሳዊና ሐዋርያዊ ትምህርተ ሃይማኖት፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን፣ በያሬዳዊ ጣዕመ ዜማ የታጀበ ሥርዐተ አምልኮ፣ በጽሑፍና በትውልድ ቅብብሎሽ የተወረሰ የረጅም ጊዜ ትውፊት ባህልና ታሪክ

  • በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የበለጸገ፣ እግዚአብሔርን የሚወድና የሚፈራ ለእግዚአብሔር የሚታዘዝና ምክረ ካህን የሚቀበል ከስልሳ ሚልዮን በላይ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ

  • ለምጣኔ ሃብት ዕድገት እጅግ የምትጠቅም በውብ ሥነ ተፈጥሮና በሥነ ጽሑፍ፣ በሥነ ጥበብና በኪነ ጥበብ፣ በታሪክና በቅርስ ሃብት የበለጸገች እንዲሁም በሃይማኖት፣ በነጻነትና በአንድነት የደመቀች ሃገር

  • የእግዚአብሔርን ቃል ከሃገር ውስጥ ባሻገር ለመላው ዓለም ማዳረስ የሚችሉ ከግማሽ ሚልዮን ያላነሱ ሊቃውንት፣ ቀሳውስት፣ ዲያቆናት፣ ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ከሁለት ሺሕ ያላነሱ ገዳማት

  • መላውን ዓለም እያዳረሰና እየሰፋ የሚገኝ ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ የተዋቀረ ጠንካራ መዋቅር ያላት መሆኗ

ያግኙን

+251 111 55 0098 P.O.Box 1283 A.A. 5 KILLO, ADDIS ABABA, ETHIOPIA በፌስቡክ ያግኙን የዩትዩብ ቻነል