ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
በውጭ አገር ለምትገኙ አህጉረ ስብከት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተላለፈ መልዕክት
ለሁለተኛ ጊዜ በውጭ አገር ለሚገኙ አህጉረ ስብከት ጥሪ ተላልፏል።ስለሆነም በተላለፈው ጥሪ መሰረት ዝርዝራችሁ ከዚህ ደብዳቤ ጋር የተለጠፈው አህጉረ ስብከት በአስቸኳይ ሪፖርታችሁን እንድታቀርቡና በገጉባኤው ላይ እንድትሳተፉ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን ።
የመስቀል ደመራ በዓል የቅድመ ዝግጅት ሥራ በአምስት ማዕከላት በመከናወን ላይ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል የቅድመ ዝግጅት ሥራውን እያከናወነ ነው።
በዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የደረሰውን ዝርፊያ በተመለከተ አሰፈላጊው ክትትል እየተደረገ ነው።
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሚገኘው የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም በትላንትናው እለት ማንነታቸው ባልታወቁ ዘራፊዎች የደረሰበትን ዝርፊያ በተመለከተ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስፈላጊውን ክትትልና ማጣራት በማድረግ ላይ የምትገኝ ሲሆን በጉዳዩ ዙሪያም ከሚመለከታቸው የመንግሥት የጸጥታ አካላት ጋር እየተነጋገረችበት ነው።
የቅድስት ልደታ ጤና ኮሌጅ በተከታታይ ዓመታት ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ።
የቅድስት ልደታ ጤና ኮሌጅ በተከታታይ ዓመታት ያስተማራቸውን ተማሪዎች ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ በተገኙበት አስመረቀ።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የ፳፻ ፲ወ፮ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል አከባበር የዝግጅት ሥራ ግምገማ ተካሔደ ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በ፳፻፲፭ ዓ/ም የሥራ ዓመት በነበረው የሥራና የአገልግሎት አፈጻጸም ዙሪያ አጠቃላይ የጠቅላይ ጽ/ቤቱ ሠራተኞች በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አሥኪያጁ በብፁዕ አቡነ አብርሃም መሪነት በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ሠፊ ውይይት አደረጉ።
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤ ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዓውደ ዓመት ዘዕስራ ምእት ዐሠርቱ ወስድስቱ ዓመተ ምሕረት
አዲሱ ዓመት የሰላምና የፍቅር፣ የዕርቅና የይቅርታ የተፈናቀለው ወደቀየው የሚመለስበት፣ ሆድ የባሰው የሚጽናናበት፣ ፍትሕና ርትዕ የሚሰፍንበት የመሳሪያ ድምፅ የማይሰማበት ፍጹም የተግባቦት ዓመት እንዲሆንልን እየጸለይን ሁሉም ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን ለዚህ ቅዱስ ጥሪ አዎንታዊ መልስ እንድትሰጡ አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም በድጋሚ እናስተላልፋለን፡፡
የመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በ ፳፻፲፭ ዓ/ም አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት አካሄዱ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በ፳፻፲፭ ዓ/ም የሥራ ዓመት በነበረው የሥራና የአገልግሎት አፈጻጸም ዙሪያ አጠቃላይ የጠቅላይ ጽ/ቤቱ ሠራተኞች በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አሥኪያጁ በብፁዕ አቡነ አብርሃም መሪነት በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ሠፊ ውይይት አደረጉ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልጅ ያሬድ በተባለው ግለሰብ እና ተባባሪዎቹ ላይ ክስ እንዲመሠረት ለፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ ጥያቄ አቀረበች።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልጅ ያሬድ በተባለውን ግለሰብ እና በተባባሪዎቹ ላይ ክስ እንዲመሠረት ለፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ በላከችው ደብዳቤ ጠይቃለች።
“ቤተክርስቲያን የተፈተነችበት ሥርዓቷን እና ልጆችዋን ያጣችበት ጊዜ ስለሆነ ለሀገራችን እና ለቤተ ክርስቲያናችን ሰላም እንዲመጣ የጷጉሜን ፮ቀናት ወደ እግዚአብሔር እንጸልይ።” ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የጷጉሜን ፮ ቀናት ጸሎተ ምህላ እንዲኖር አወጀ።
ልጅ ያሬድ የተባለውን ግለሰብ በህግ ለመጠየቅ የሚያስችል ሥራ እየተሰራ ነው።
ነሐሴ ፳፮ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም