ልማት በቤተ ክርስቲያን
ልዮ ዕትም መጽሔት
ይህ ”ልማት በቤተክርስቲያን“ የተሰኘ ልዮ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
ለሁለት ቀናት ሲሰጥ የነበረው የህዝብ ግንኙነት የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተጠናቀቀ።
በሥልጠናው መዝጊያ ላይ የተገኙት ብጹዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በህዝብ ግንኘነት አስፈላጊነትና ለቤተክርስቲያን ያለውን ፋይዳ በዝርዝር ገልጸው ቤተክርስቲያን በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን በህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ዘመኑን የዋጀና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ሥራ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።
የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዓለ ንግስ ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በታላቅ መንፈሳዊ ሥነሥርዓት ተከብሮ ዋለ።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖትና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዓለ ንግሥ በአዲስ አበባ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ዛሬ ሚያዝያ ፳፫ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ,ም በከፍተኛ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ተከበረ ።
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ “አሜን ኢትዮጵያ” የተሰኘ የበጎ አድራጎት ድርጅት ባተዘጋጀ መርሐ ግብር ላይ ተገኝተው የሰላም መልእክት አስተላለፉ ።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና ከሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ጋር በመሆን በሰበታ ጌተሴማኒ ገዳም በመገኘት የ፳፻ ፲ወ፭ዓ,ም የትንሣኤ በዓልን አከበሩ።
ቅዱስነታቸው በሰበታ ጌተሰማኒ ጠባባት ገዳም ከሚገኙ ሕጻናት ጋር የፋሲካን በዓል አከበሩ።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና ከሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ጋር በመሆን በሰበታ ጌተሴማኒ ገዳም በመገኘት የ፳፻ ፲ወ፭ዓ,ም የትንሣኤ በዓልን አከበሩ።
ከወደቅንበት የራስን ጥቅም የማሳደድ አዚም ወጥተን የቤተ ክርስቲያንን ህልውና ሊያጸና የሚችለውን ሥራ እያስቀደምን ማገልገል የሁላችንም ውሳኔ መሆን እንዳለበት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አሳሰቡ።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዛሬ ሚያዝያ ፱ቀን ፳፻ ፲ወ፭ዓ.ም በጠቅላይ ቤተክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ በተካሄደው የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር ላይ ያስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል።
የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የትንሣኤ በዓልን ምክንያት የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር ተካሔደ።
በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ክቡር ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የየመምሪያና የየድርጅቶቹ የሥራ ኃላፊዎች ክቡር ሊቀ አእላፍ በላይ ጸጋዬ የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ፣የአድባራትና ገዳማት ከስተዳዳሪዎች እና የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።
በቂም፣ በበቀል፣ በጥላቻ ወድቀን ትንሣኤውን እናከብራለን ማለት ትክክል እንዳልሆነ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ተናገሩ።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ብርሃነ ትንሣኤው የሰላም፣ የሕይወት፣ የጤና፣ የበረከትና የፍቅር ይሆን ዘንድ ተመኝተዋል፡፡
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ለ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የትንሳኤ በዓል ያስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ሙሉ ቃል እነሆ፤
የገብረ ሰላመ በዐል በታላቅ ድምቀት ተከበረ።
የ፳፻ ፲ወ ፭ ዓ.ም የገብረ ሰላመ በዐል በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፣ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ክቡር ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት መ/ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የጠቅላይ ቤተክህነት የየመምሪያውና የየድርጅቶቹ ኃላፊዎች፣ክቡር ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ ጸጋዬ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ አምባሳደር ሬሚ Remi Marechaux በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር፣የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ምዕመናንና ምዕመናት በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ሥነሥርዓት ተከብሯል።
የሆሳዕና በዓል በተለያዩ አህጉረ ስብከት በታላቅ ሃይማኖታዊ ሥርዓት በድምቀት ተከበረ።
የሆሣዕና በዓል በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሯል።