ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በባህርዳር ሀገረ ስብከት የሚከናወኑ ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ፣ወደፊት በሚሰሩ የልማት ሥራዎች ዙሪያም የሥራ መመሪያ ሰጡ።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከሚያዝ ፰ -፲፩ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም በሀገረ ስብከታቸው ውስጥ ያስጀነመሯቸውን ሕንፃ አብያተ ክርስቲያናትና ልዩልዩፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል ። በፕሮጀክቶቹ ዙሪናም ድጋፍና ክትትልም አድርገዋል፣ ከገዳማትና አድባራት አስተዳደር ክፍሎች ጋርም ውይይት አካሂደው የሥራ መመሪያና ወደፊት መአናወን በሚገባቸው ሥራዎች ዙሪያም አቅጣጫ ሰጥተዋል።

ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ በጀርመን ከሙንስተር የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ጋር ውይይት አደረጉ።

ብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የጀርመንና አካባቢው እና የምሥራቅ ጎጃም አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መጋቢት ፭ ቀን ፳፻፲፭ ዓ ም በጀርመን ሙንስትር ከተማ በመገኘት ከካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን የሙንስተርና አካባቢ ጳጳስ ከኾኑት ዶክተር ፊልክስ ጌን ጋር ውይይት ውይይት ማድረጋቸውን የሀገረ ስብከቱ ሕዝብ ግንኙነት ክፍል በላከልን ዘገባ ገልጿል።

ቅዱስ ሲኖዶስ መጋቢት ፳፩ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ምልአተ ጉባኤ እንዲካሄድ ጥሪ ተላለፈ

በህገ ወጥ መንገድ የተሾሙት ግለሰቦች በአምስት ቀናት ውስጥ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት መገኘት ሪፖርት እንዲያደርጉ ጥሪ አስተላለፈ።

በምሥራቅ አውሮፖ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ተባርኮ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።

በፖላንድ ዋና ከተማ ዋርሶው ከተማ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ዲዮናስዮስ የምሥራቅ ጎጃም፣ የጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተባርኮ አገልግሎት ጀምሯል ።

የመምህር የኔታ ሐረገወይን ምሕረቱ የሽኝት መርሐ ግብር

የመምህር የኔታ ሐረገወይን ምሕረቱ የሽኝት መርሐ ግብር ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣የጠቅላይ ቤተክህነት የምምሪያ ኃላፊዎች የመንግስት ባለሥልጣናት፣የባቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባና ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት በዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ተፈጸመ።

ወላዴ አእላፍ መምህር የኔታ ሐረገ ወይን ምሕረቱ የሕይወት ታሪክ

ወላዴ አእላፍ መምህር የኔታ ሐረገ ወይን ምሕረቱ በወሎ ክፍለ ሀገር ሰገራት (ኩታበር ወደ ግሸን መሔጃ) ከወላጅ አባታቸው ከአለቃ ምሕረቱ ካሣ ከእናታቸወ ወ/ሮ አበቡ ወልደ ጻድቅ በየካቲት 16 ቀን 1916 ዓ.ም ተወለዱ። የፊደልና ንባብ ትምህርት የጀመሩት በእናታቸው ሀገር በቦሩ ሥላሴ ነው።

ፍርድ ቤቱ የሕገወጥ ቡድኑን መቃወሚያዎች ሙሉ በሙሉ ውድቅ በማድረግ ቤተ ክርስቲያን ከጠየቀችው ዘጠና ቀናት ውስጥ የ፵፭ ቀናት የእግድ ትዕዛዝ ወሰነ።

የካቲት ፴/፳፻፲፭ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

በቦረና በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ የማሰባሰብ እንቅስቃሴውን የሚያስተባብሩ በብፁዓን አባቶች የሚመራ አምስት አባላት ያሉት ዐቢይ ኮሚቴ ተመደበ፤

. . . በሦስት ብፁዓን አባቶች እና በሁለት የጠቅላይ ቤተክህነት የሥራ ኃላፊዎች የሚመራ ዐቢይ ኮሚቴ እንዲዋቀርና ወደ ሥራ እንዲገባ ያስተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ውሳኔውን እንዲያስፈጽም ኃላፊነት ሰጥቷል።

የጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጉባኤ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/መገናኛ ብዙሃን ሥርጭት ድርጅትና የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በሰው ሃይል እንዲጠናከሩ ወሰነ።

. . . በቀጣይ ጊዜ በሁለቱ ተቋማት በጥምረትና በተናጠል መሰራት ያለባቸው ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎችን ጉባኤው ያመላከተ ሲሆን በተለይም መረጃዎችን የማሰባሰብ፣ወቅታዊ ምላሽ የመስጠትና በየዕለቱ የዜና ሽፋን የመስጠት ጉዳይ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራ አቅጣጫ አስቀምጧል።

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፬ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፩ኛ ዓመት መታሰቢያ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከናወነ።

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ፬ኛ ዓመታ መታሰቢያ በመንበረ ጸባዖት ቅድስ ስላሴ ካቴድራል ብፁዕአን ሊቃነ ጳጳሳት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የሥራ ኃላፊዎች፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ሊቃውተ ቤተክርስቲያን ወዳጆቻቸው እና የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል።

በፌስቡክ ያግኙን

የኅትመትና ሚዲያ ዋና ክፍል

ብፁዕ አቡነ አብርሃም

የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ

በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ

ለውስጥ አገልግሎት

የኢሜይል አገልግሎት

ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን

ርእይ

ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት

ተልእኮ

  • የእግዚአብሔርን ቃል ለሰው ልጆች ሁሉ ማስተማርና ማዳረስ

  • ሰውን በሁለንተናዊ ሰብእናው ማገልገልና ማዳን

  • ሰውን ሁሉ በነገረ መለኮትና በነገረ ጥበብ ትምህርት በማልማት በመንፈሳዊም ሆነ በሥጋዊ ሕይወቱ የተሻለ ኑሮ እንዲኖረው ማድረግ

  • ጥራትና ብቃት፣ ፍትሐዊነትና እኩል ተደራሽነት ያለው መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ለሰው ሁሉ ማበርከት

  • የተለያዩ የልማት መርሀ ግብሮችን በመንደፍ ቤተ ክርስቲያንን በኢኮኖሚ ማበልጸግ

  • በቴክኖሎጂ ስልት የሚመራና አዋጭነቱ አስተማማኝ የሆነ የጠቅላላ ሀብት አስተዳደርና አጠቃቀም እንዲረጋገጥ ማድረግ

  • የሰው ልጆች ሁሉ እኩልነት፣ ሰላምና ፍትሕ፣ ፍቅርና ስምምነት እንዲጠበቅ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ

  • የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አሰራር ግልጽ፣ ለሁሉም ተደራሽና ችግር ፈቺ እንዲሆን ማድረግ

ዕሴቶች

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅሊናን የሚረታ፣ አእምሮን የሚመሥጥ፣ ከጥንተ ፍጥረት ተነሥቶ በዘመነ አበው በሕገ ልቡና፣ በዘመነ ብሉይ በሕግ ኦሪት፣ ተራምዶ መዳረሻውን ሕገ ወንጌል ያደረገ ጥንታዊ ክርስቶሳዊና ሐዋርያዊ ትምህርተ ሃይማኖት፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን፣ በያሬዳዊ ጣዕመ ዜማ የታጀበ ሥርዐተ አምልኮ፣ በጽሑፍና በትውልድ ቅብብሎሽ የተወረሰ የረጅም ጊዜ ትውፊት ባህልና ታሪክ

  • በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የበለጸገ፣ እግዚአብሔርን የሚወድና የሚፈራ ለእግዚአብሔር የሚታዘዝና ምክረ ካህን የሚቀበል ከስልሳ ሚልዮን በላይ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ

  • ለምጣኔ ሃብት ዕድገት እጅግ የምትጠቅም በውብ ሥነ ተፈጥሮና በሥነ ጽሑፍ፣ በሥነ ጥበብና በኪነ ጥበብ፣ በታሪክና በቅርስ ሃብት የበለጸገች እንዲሁም በሃይማኖት፣ በነጻነትና በአንድነት የደመቀች ሃገር

  • የእግዚአብሔርን ቃል ከሃገር ውስጥ ባሻገር ለመላው ዓለም ማዳረስ የሚችሉ ከግማሽ ሚልዮን ያላነሱ ሊቃውንት፣ ቀሳውስት፣ ዲያቆናት፣ ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ከሁለት ሺሕ ያላነሱ ገዳማት

  • መላውን ዓለም እያዳረሰና እየሰፋ የሚገኝ ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ የተዋቀረ ጠንካራ መዋቅር ያላት መሆኗ

ያግኙን

+251 111 55 0098 P.O.Box 1283 A.A. 5 KILLO, ADDIS ABABA, ETHIOPIA በፌስቡክ ያግኙን የዩትዩብ ቻነል