የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በባሻ ወልዴ ችሎት የግንባታ ሥራው የተጠናቀቀውን ሕንጻ ቁልፍ ተረከቡ።

April 7, 2023

መጋቢት ፳፱ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ዓ.ም
*****
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የኢኮኖሚ አቅሟን በተለያዩ የልማት ሥራዎች በማጎልበት ተቀዳሚ ተልዕኮዋ የሆነውን ስብከተወንጌልን ማስፋፋት፣የገጠር አብያተክርስቲያናትን የማጠናከር፣የአብነት ትምህርት ቤቶችን የማስፋፋትና የማጠናከር ሥራዋን ለማቀላጠፍ ያስችላት ዘንድ በተለምዶ ባሻ ወልዴ ችሎት በመባል በሚታወቀው ቦታ ላይ በአንድ ዓመት ውስጥ ያስገነባችው ዘመናዊ አፓርታማ ተጠናቆ በዛሬው ዕለት የቁልፍ ርክክብ ተደርጓል።

በርክክብ ሥነሥርዓቱ ላይ የተገኙት ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቤተክርስቲያን ከመንፈሳዊ አገልግሎቷ በተጓዳኝ በተለያዩ የልማት ዘርፎች በመሰማራትና ኢኮኖሚያዊ አቅሟን በማሳደግ በመንፈሳዊው ዘርፍ ውጤታማ ሥራዎችን እያከናወነች መሆኗን ገልጸዋል።

ቤተክርስቲያን በሕንጻ ግንባታዎች ላይ በመሰሚራቷም ለበርካታ ወገኖች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር በርካታ ወገኖችን መጥቀሟን የገለጹት ብፁዕነታቸው በቤት ችግር ምክንያት የሚንገላቱ ወገኖችም የመኖሪያ ቤት የሚያገኙበትን ዕድል ከመፍጠር አልፋ ለከተማችን አዲስአበባ ገጽታ ግንባታም ዓይነተኛ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች ብለዋል።

ዛሬ የቁልፍ ርክክብ የሚደረግለት ይህ ሕንጻ በብፁዕ አቡነ ያሬድ የጠቅላይ ሥራ አስኪያጅነት ጊዜ ተጀምሮ በአንድ ዓመት ውስጥ በመጠናቀቁ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸው ቀደም ተብለው የተጀመሩና የግንባታ ሥራቸው በልዩ ልዩ ምክንያቶች የተጓተቱት ሁለት ሕንጻዎችን በተቻለ ፍጥነት ለማጠናቀቅ የሚያስችል ሥራ የተሰራ በመሆኑ በቅርብ ጊዜ የግንባታ ሥራቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት እንደሚበቁ ያላቸውን ተስፋ ገልጸው አሁን የተጠናቀቀው ሕንጻም በህጋዊ የጨረታ ሥርዓት ለተጠቃሚዎች ይተላለፋል ብለዋል።

በአንድ ዓመት ውስጥ የግንባታ ሥራው ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ የሆነው ይኸው ህንጻ 21ክፍሎች ያሉት እያንዳንዱ ክፍልም 3 መኝታ ቤቶች፣ ሊፍትና ጄኔሬተር ያለው ሲሆን ቴራሱ በሕንጻው ላይ ለሚኖሩ ነዋሪዎች ልዩልዩ ዝግጅቶች የሚያገለግል ይሆናል፤ከዚህ በተጨማሪም ሕንጻው የእሳት ማጥፊያ እና የውሀ ፓንፕ የተገጠመለትና ከወዳጅነት ፓርክ ፊለፊት ለመኖሪያ ምቹ በሆነ ሥፍራ ላይ የሚገኝ ሕንጻ ነው።

የሕንጻ ግንባታ ሥራውም በአተም ኮንስትራክሽንና በዘዶር አማካሪ ድርጅት የተገነባ ሲሆን ለዚህ ሕንጻ ግንባታ በታቀደለት ጊዜ መጠናቀቅም የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅና የሥራ ኃላፊዎች ሚና የጎላ ነው።

ብፁዕ አቡነ ያሬድ በዘመነ ሢመታቸው ይህን ሕንጻ ግንባታን ጨምሮ በድሬዳዋ ከተማ ተገንብቶ ለአገልግሎት የበቃውን ባለ አራት ወለል የገበያ ማዕከልና በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት በመገንባት ላይ የሚገኘውን ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ግንባታዎችን በማስጀመር ለብፁዕ አቡነ አብርሃም ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ማስረከባቸው ይታወሳል።

በርክክብ ሥነሥርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁን ጨምሮ ፣ም/ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ፣የጠቅላይ ቤተክህነት መምሪያ ኃላፊዎች የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የሕንጻ ሥራ ተቋራጩና የአማካሪ ድርጅቱ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

በድሬደዋ ከተማ የተገነባው ሁለገብ የገበያ ማዕከል እና በዛሬው ዕለት የቁልፍ ርክክብ የተደረገለት ህንጻ የምርቃት መርሀ ግብር ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በበዐለ ሀምሳ ውስጥ እንደሚከናወን ከቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ብፁዕ አቡነ ድሜጥሮስ የአቡዳቢ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራልን የአገልግሎት ፈቃድ ሰነድ ተረከቡ። Link to: ብፁዕ አቡነ ድሜጥሮስ የአቡዳቢ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራልን የአገልግሎት ፈቃድ ሰነድ ተረከቡ። ብፁዕ አቡነ ድሜጥሮስ የአቡዳቢ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም... Link to: በምስራቅ አፍሪካ ሀገረ ስብከት በሱዳን መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የተከሰተውን አለመግባባት አጥንተው የውሳኔ ሀሳብ የሚያቀርቡ የሥራ ኃላፊዎች ካርቱም ገቡ። Link to: በምስራቅ አፍሪካ ሀገረ ስብከት በሱዳን መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የተከሰተውን አለመግባባት አጥንተው የውሳኔ ሀሳብ የሚያቀርቡ የሥራ ኃላፊዎች ካርቱም ገቡ። በምስራቅ አፍሪካ ሀገረ ስብከት በሱዳን መድኃኔዓለም...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top