የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

በቂም፣ በበቀል፣ በጥላቻ ወድቀን ትንሣኤውን እናከብራለን ማለት ትክክል እንዳልሆነ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ተናገሩ።

April 15, 2023

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ብርሃነ ትንሣኤው የሰላም፣ የሕይወት፣ የጤና፣ የበረከትና የፍቅር ይሆን ዘንድ ተመኝተዋል፡፡

“ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጋላችሁ፣ ተነስቷል እንጂ በዚህ የለም፣ የሰው ልጅ በሐጥያተኞች እጅ ተላልፎ ሊሰጥና ሊሰቀል፣ በሦስተኛውም ቀን ሊነሳ ግድ ነው እያለ እንደተናገረ አስቡ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስን ሞት ይዞ የሚያስቀረው አይደለም ብለዋል፡፡ በሞት ላይ ስልጣን ያለው፣ በሞቱ ሞትን የገደለ፣ በሞቱ ነጻነትን የሰበከ፣ በሲኦል ያሉትን የፈታ ሲኦልን የገለባበጠ፣ ዲያቢሎስን ያሰረ ሕያው ነውም” ብለዋል ብፁዕነታቸው፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ታላቁን ፆም በፆምና በስግደት ካሳለፈች በኋላ የተቀበለውን መከራ በማሰብ ትንሣኤውን እንደምታከብርም ተናግረዋል፡፡ የክርስቶስ ትንሣኤ የሁላችንም ትንሣኤ ነው ያሉት ብፁዕ አቡነ አብርሃም የክርስቶስ ትንሣኤ ሁላችንን ይገዛ የነበረው ሞት የተሸነፈበት ነውም ብለዋል፡፡

ክርስቶስ ለሰው ልጅ ቸርነቱን ያደረገበት፤ በንጹሕ ደሙ የዋጀበትና የራቀውን ሁሉ ያቀረበበት በመሆኑ ትንሣኤውን በልዩ ሁኔታ እናከብረዋለንም ነው ያሉት፡፡ ከእርሱ ጋር ሳለን ደስታና ሰላም አለን፣ በዓለም ግን መከራ አለ ብለዋል፡፡ የዓለምን ፍላጎትና ምኞት ለማሟላት በተሄደ ቁጥር መከራዎች መኖራቸውን ተናግረዋል።፡፡

አምላክ ዓለምን ያሸነፈበት ጥበቡ እጅግ ድንቅ ነው ያሉት ብፁዕነታቸው የእርሱን ፈለግ የተከተ ሁሉ ዓለምን እና ፈተናዋን ያሸንፋልም ብለዋል፡፡ ክርስቶስ ጦርን በጦር ሳይሆን በፍቅር፣ በሰላም እና በትዕግስት ማሸነፉንም ተናግረዋል፡፡ ክርስቶስ ዓለምን በትዕግስት፣በሰላም በፍቅርና በአንድት እንዳሸነፈ ሁሉ እኛም ሰላም ይኑረን ከዚህ ውጭ ያለው ትርጉም የለውም ነው ያሉት፡፡

ዓለም በጥላቻ ተበክላለች ያሉት ብፁዕነታቸው ብዙዎች በሚያደርጉት አላስፈላጊ ፉክክር ዓለም እየተመሰቃቀለች ንጹሐን እየተጎዱ መሆናቸውንም ገልጸዋል፡፡ ትንሤኤውን የምሥራች የምንባባል ሁሉ ለሰለም ቅድሚያ መስጠት ግድ ይላል ነው ያሉት፡፡ መከራ የበዛባትን ዓለም መሻገር የሚቻለው በመደማመጥ፣ በመቀራረብ እና በመነጋር መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ጦርና ጦርነት፣ መግደልና መሳደድ ትርጉም እንደሌላቸውም አስረድተዋል፡፡ አላስፈላጊ ውጣ ውረዶች፣ አላስፈላጊ አሸንፍ ባይነት፣ አላስፈላጊ ስምና ዝና ንጹሐንን እየጎዳ መሆኑንም አንስተዋል፡፡

በቂም፣ በበቀል፣ በጥላቻ ወድቀን ትንሣኤውን እናከብራለን ብንል ለምንም አይጠቅመንም ነው ያሉት፡፡ ከሙታነ ሕሊና መራቅ እንደሚገባ ያሳሰቡት ብፁዕ አቡነ አብርሃም ሙታነ ሕሊና ሰላም የጎደላቸው፤ ከጥላቻ ሌላ የማያውቁ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ መተዛዘን፣ በጋራ መብላት እና መጠጣት ግድ እንደሚልም ገልጸዋል፡፡

ከመከራው ለመዳን ማሸነፊያ መንገዱን ከእርሱ እንማርም ብለዋል፡፡ ጥላቻና መጥፎ ሃሳብ በምድር ላይ እንዳይነግሥ ፍቅርን ገንዘብ ማድረግ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡ መልካም ያደረጉት መልካም ትውልድና መልካም ሀገር ማቆየታቸውንም ገልጸዋል፡፡ በሀገሩ ስደተኛ፣ መጻተኛ፣ ተፈናቃይ፣ በስጋት የሚንከራተት እንዳይኖር እና ሰላም ይበዛ ዘንድ ሕያው የሆነውን አምላክ እንጠይቀው ነው ያሉት ብፁዕነታቸው፡፡

በዓለ ትንሣኤው ሲከበር የታመሙትን በመጎብኘት፣ የተራቡትን በማብላት፣ የተጠሙትን በማጠጣት፣ የተቸገሩትን በመርዳት፣ በሰላም እና በፍቅር ሊሆን እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡

© ፈለገ ገነት ሚዲያ

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ Link to: ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ Link to: የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የትንሣኤ በዓልን ምክንያት የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር ተካሔደ። Link to: የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የትንሣኤ በዓልን ምክንያት የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር ተካሔደ። የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የትንሣኤ በዓልን ምክንያት የእንኳን...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top