ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
ብፁአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በመሪ ምሥራቀ ጸሐይ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ተገኝተው የሕንፃ ግንባታው ሒደት ጎበኙ።
ታኅሣሥ 7 ቀን 2016 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ የባሕር ዳርና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ጸሓፊና የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት እና የደቡብ ኦሞ ጅንካ ፣ የአሪ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ብፁዕ አቡነ ሰላማ የምዕራብ ጎንደር ሊቀ ጳጳስ እንዲሁም መልአከ ምሕረት ዘካርያስ ሐዲስ የየካና ለሚ ኩራ ክፍላተ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ በመሪ ምሥራቀ ጸሐይ ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ተገኝተው የሕንፃ ግንባታው ሒደት ጎብኝተው መንፈሳዊ አገልግሎት ሰጥተዋል።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም በእስራኤል የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎት አጠናቀው ወደ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ተመለሱ።
የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ለሚያስገነባው ባለ ዐስራ ሁለት ወለል ሕንጻ ገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ኅዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም በግራንድ ኤልያና ሆቴል አካሂዷል።
ማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ባከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ከ7.5 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡
የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ለሚያስገነባው ባለ ዐስራ ሁለት ወለል ሕንጻ ገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ኅዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም በግራንድ ኤልያና ሆቴል አካሂዷል።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከእስራኤል የቱሪዝም ሚንስትር ጋር ተወያዩ፤የእስራኤል ሙዝየምንም ጎበኙ።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በቅድስት አገር ኢየሩሳሌም የሚያደርጉትን ሐዋርያዊ አገልግሎት ቀጥለዋል።
በወቅታዊ ጉዳዮች ከቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
“ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ፥ ወይስ ጭንቀት፥ ወይስ ስደት፥ ወይስ ራብ፥ ወይስ ራቁትነት፥ ወይስ ፍርሃት፥ ወይስ ሰይፍ ነውን? ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን፥ እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን” ሮሜ 8፡35-36
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የሐዋርያዊ አገልግሎት መዳረሻቸው እስራኤል ገብተዋል።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፥ የባህር ዳርና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ዻዻስ በእስራኤል ቴልአቪቭ ቤንጎርዮን ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት ሊቀ ጳጳስና የገዳማቱ አበው መነኮሳት ደማቅ አቀባባል አድርገውላቸዋል።
በሲነርጂ ሀበሻ ፊልምና ኮሚኒኬሽን በመዘጋጀት ላይ የሚገኘው የሰማዕቱ ሊቀ ጳጳስ የብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ፊልም ጽሑፍ በሊቃውንት ጉባኤ እንዲመረመር ታዘዘ።
የፊልሙ ጸሐፊ እና ዳይሬክተር ሞገስ ታፈሰ ዶ/ር እየተዘጋጀ የሚገኘውን ፊልም ቤተክርስቲያናችን በሊቃውንቶቿ አማካኝነት መርምራ፣ የሚታረም ካለ አርማና የሚቃናውን አቅንታ በምትሰጠን አስተያየትና ማስተካከያ መሠረት ፊልሙን የምንሠራ መሆኑ ታውቆ አስፈላጊው ትብብር ሁሉ ይደረግልን። በማለት በጽሑፍና በአካል ጠቅላይ ቤተ ክህነት በመገኘት በፊልሙ ዝግጅት ዙሪያ ማብራሪያ በመስጠት ለተፈጠረው የመረጃ ክፍተት ይቅርታ ጠይቀዋል።
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት መፍትሔ ሊሰጥባቸው ይገባል ያላቸውን በ13 ነጥቦች የተዘረዘሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በሀገረ ስብከቱ በኩል መፍትሔ እንዲሰጣቸው ውሳኔ አስተላለፈ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጋር ባደረገው ውይይት በሀገረ ስብከቱ በኩል የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በተመለከተ በተደረገው የጋራ ውይይት በሀገረ ስብከቱ የሚስተዋሉትን ዋናዋና ችግሮች መቅረፍ ይቻል ዘንድ በጠቅላይ ቤተክህነት በኩል ተለይተው የሚታወቁት ዋናዋና ነጥቦች ለሀገረ ስብከቱ እንዲደርሰው ተደርጎ መፍትሔ እንዲሰጥበት የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሔኖክ በጉባኤው ወቅት በሰጡት ማጠቃለያ ሀሳብ ላይ በገለጹት መሰረት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ ኅዳር 24ቀን2016ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ ሀገረ ስብከቱ በኩል በአፋጣኝ ምላሽ ሊያገኙ ይገባቸዋል ያላቸውን 13 ነጥቦችን በመለየት ለሀገረ ስብከቱ እንዲደርሰውና ከበዛ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለተጠቀሱት የመልካም አስተዳደር ችግሮች ምላሽ እንዲሰጥና የውሳኔውን መፈጸም አለመፈጸም በተመለከተም ተከታትለው የሚያስፈጽሙ ሦስት የመምሪያ ኃላፊዎችን መድቧል።
በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የተፈጸመውን ግድያ የጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር ጉባኤ አወገዘ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር ጉባኤ በዛሬው እለት ባደረገው መደበኛ ስብሰባ በምሥራቅ አርሲ አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ላይ የደረሰውን የሞት አደጋ በተመለከተ ኅዳር 24 ቀን 2016ዓ.ም ከሀገረ ስብከቱ በስልክና በደብዳቤ የደረሰውን መረጃ መነሻ በማድረግ ውይይት ካደረገ በኋላ ውሳኔ አስተላልፏል።
በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የተፈጸመውን ጥቃት በማስመልከት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የተሰጠ መግለጫ ፤
በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት በጥብቅ እናወግዛለን፤የጸጥታ ተቋማትም ጥቃቱን እንዲከላለሉ እንጠይቃለን።