የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

“ለቤተክርስቲያን አይደለም ጥቅማጥቅማችንን አንገታችን እንሰጣለን” ብፀዕ አቡነ አብርሃም

September 9, 2024

ጷጉሜን ፬ ቀን ፪፻፲፮ ዓ.ም.
__________

የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ “አዲሱን ዓመት በመንፈስ ዝግጅት እንቀበል” በሚል መሪ ቃል በጽርሐ ተዋሕዶ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ አዘጋጀ።
ጉባኤው ከጠዋቱ 2:30 ላይ የተጀመረ ሲሆን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፀዕ አቡነ አብርሃም፣ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ፣ የምዕራብ ሐረጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እንጦንስ ፣ የአዊ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቶማስ፣ የሲዳማ ሀገረ ስብከትና የታቦር ፍኖተ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ፣ የማዕከላዊ ጎንደር ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ ፣ የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ዋና ኀላፊ ክቡር መልአከ ሰላም አባ ቃለጽቅ ሙሉ ጌታ (ዶ/ር) የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የየመምሪያ ኀላፊዎች፣ሠራተኞች እና የአዲስ አበባ ማዕከል የማኅበረ ቅዱሳን ዘማርያን እንዲሁም የፍኖተ ጽድቅ ማኅበር ዘማርያን በተገኙበት ተካሂዷል።

በመርሐግብሩ መጀመሪያ ላይ የመ/ፓ/ጠ/ቤ/ካህናት መምሪያ ኃላፊ ክቡር ሊቀ ካህናት እንቖባሕርይ ተከስተ የሬዳዊ ዜማ ያቀረቡ ሲሆን በመቀጠልም የማኅበረ ቅዱሳን አዲስአበባ ማዕከል ዘማርያን ዝማሬ አቅርበዋል የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ አዲሱን ዓመት በአዲስ መንፈስ ለመቀበል የጋራ ጸሎትና ትምህርት እንዲኖር በማሰብ ያዘጋጀው ሲሆን ዋና ዓላማው በእምነት ፣ በንቃትና በተጋት ተሻግሮ አዲሱን የቸርነቱን ስጦታ ለመቀበል እንድንችል ማንቃት መሆኑን የመምሪያው ዋና ኀላፊ ገልጸዋል። አዲሱን ዓመት በአዲስ ሕይወት ፍትሕና ርትዕ የሰፈነበት አገልግሎት እንዲኖረን ለማስታወስ የተዘጋጀ መርሐግብር መሆኑን ኀላፊው አክለው ገልጸዋል። በመቀጠልም የመምሪያው ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የመግቢያ ንግግር ሲያደርጉ በመሪ ቃሉ የተጠቀሰውን ቃል ከማብራራት ጀምረዋል። “መንፈስ” ስንል በምስጢራዊ ፍች ሲፈታ “ቅን ልቡና” ማለታችን ነው ብለዋል። በመንፈስ መታደስ ማለት አዲስ ቁሳቁስ መግዛት ሳይሆን ልብን ማደስ ማለት ነው ብለዋል። አዲሱን ዓመት የዓለም ሐሳብ ባላጣመመው በቅን ልቦና ልንቀበለው ይገባል የሚል መልእክት አስተላልፈዋል።

በመቀጠልም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፀዕ አቡነ አብርሃም የተዘጋጀው መርሐግብር ያሳለፍነውን ዓመት በመዳሰስ የወደፊቱን በአዲስ መንፈስ እንድንቀበል የሚያነቃ መሆኑን በመግለጽ ከመጽሐፍ ቀዱስ ሁለት ጥቅሶችን በማንሳት ያለፈውን ጊዜ ለማዘከር የሚመጣውን ለማቀድ እንዲቻል አስትመረዋል። ለነቢዩ ዮናስ የተሰጠውን አምላካዊ ትዕዛዝ “ወደ ታላቂቱ ከተማ ሂደህ ስበክ” የሚለውንና የጌታችንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ትምርህት “ሙታናቸውን እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው አንተ ግን የእግዚአብሔርን መንግሥት ስበክ” የሚለውን በማንሳት ይህንን አምላክዊ መመሪያ በማክበር በአዲሱ ዓመት ስብከትን የዘወትር ሥራችን እንዲሆን መክረዋል። በአዲሱ ዓመት አይደለም ጥቅማጥቅም አንገታችን ለቤተክርስቲያን መስጠት መገለጫችን ነውና በርትተን ይህንን ማስቀጠል ይኖርብናል ብለዋል።

በመቀጠለም የሲዳማ ሀገረ ስብከትና የታቦር ፍኖተ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሊቀ ጳጳስ #ካለፈው_ዓመት_ተምረን_መጪውን_ዓመት_በመንፈስ_እንቀበል በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሑፍ አቅርበዋል። ጥናቱ ከ14 በላይ ርዕሰ አንቀፆች ያሉት ሲሆን አጽንዖት የተሰጠባቸውን ዋና ዋናዎቹን በማንሳት አብራርተዋል ። የብሔር ግጭት ፣ ጥላቻ ፣ የሰላም እጦት፣ የአስተዳደር ድክመት፣ የባሕል መቀወስ ፣ ፍትሕን ማስከበር አለ መቻል፣ የአንድነትን ስብራት መጠገን አለመቻል እና መሰል ነገሮችን በማንሳት ባሳለፍነው ዘመን ያለፉብን መሆኑን ጠቅሰው ለውጥ ማምጣት እንድንችል ግን ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ በመስጠት እና የቤተክርስቲያን አንድነትን አስጠብቀን አዲሱን ዓመት መቀበል እንዳለብን አሳስበዋል። ከጥናቱ በመቀጠል የፍኖተ ጽድቅ መንፈሳዊ ማኅበር ዘማርያን ዝማሬ አቅርበዋል ።

በመጨረሻም በስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ማርቆስ የነገይቱን ቤተክርስቲያን አፅዕንዖት ሰጥተን እንድነሠራ ማሳሰቢያ ተሰጥቶ ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ ተደርጎ የጉባኤው ፍጻሜ ሆኗል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት መካከል አንዱ የሆነው ቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት በርዕሰ አድባራት ወገዳማት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል በድምቀት ተከበረ። Link to: ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት መካከል አንዱ የሆነው ቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት በርዕሰ አድባራት ወገዳማት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል በድምቀት ተከበረ። ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት መካከል አንዱ የሆነው ቅዱስ... Link to: የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ Link to: የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለመላው የኢትዮጵያ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top