ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
፵፪ኛው የሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ተካሔደ።
የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ፵፪ኛውን አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤውን አካሔደ።የሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባዔው ከመካሔዱ አንድ ቀን ቀደም ብሎም በሀገረ ስብከቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ታላቅ ጉባኤ መካሔዱን ከሀገረ ስብከቱ የደረሰን ዘገባ ያመለክታል።
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ቤተክህነት መሆኑን በመገንዘብ ሕግና መመሪያን አክብሮ እውነትና እውነተኝነትን መርሁ አድርጎ እንዲሰራ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አሳሰቡ።
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በጋራ ለመፍታትና መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጠቅላይ ቤተክህነትና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአስተዳደር ጉባኤ አባላት በዛሬው እለት ባደረጉት የጋራ ጉባኤ ተስማሙ።
የጠቅላይ ቤተክህነትና የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት አስተዳደር ጉባዔ አባላት በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ የጋራ ጉባዔ በማድረግ ላይ ናቸው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተዳደር ጉባኤ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአስተዳደር ጉባኤ አባላት ጋር በሁለትዮሽ የአሰራር ሒደት፣በመልካም አስተዳደር፣በሕግ ፣ደንቦችና መመሪያዎች አከባበር በአጠቃላይ ሥራዎችን በተቋማዊ አሰራር ሒደት በማከናወን ዙሪያ የጋራ መድረክ ተዘጋጅቶ ውይይት እንዲደረግ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር ጉባኤ ያስተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ዛሬ ኅዳር ፲፰ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ የጋራ ጉባኤ በማካሔድ ላይ ናቸው።
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) በዓለም አብያተ ክርስቲያናት ስብሰባ እየተካፈሉ ይገኛሉ፤
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ስብሰባን ለመካፈል ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ወክለው የተጓዙ ሲሆን ስብሰባው በጄናቫ ቦሴ የቴዎሎጅ ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
ሀገራዊ ሰላምን፣ መረጋጋትንና አንድነት ማስፈንን አስመልክቶ በጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ በተላለፈው ውሳኔ መሠረት ከቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፤
“ሰላምየ አኀድግ ለክሙ ወሰላመ አቡየ እሁበክሙ፡- ሰላሜን እተውላችኋለሁ፥ የአባቴ ሰላምም እሰጣችኋለሁ” (ዮሐ.14፡27)
የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት 42ኛው ጠቅላላ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ጸሎተ ቡራኬ በይፋ ተጀመረ።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ 42ኛው የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ጠቅላላ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ የኢትዮጵያ ሃይማኖቶች ተቋማት ጉባኤ የቦርድ ሰብሳቢ ጸሎተ ቡራኬ ፡ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ልዑካን ፡ክቡር መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ፡ የሀገረ ስብከቱ የየክፍል ኃላፊዎች ፡ የየወረዳ ቤተ ክህነቱ ሊቃነ ካህናትና ሠራተኞች ፡ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፡ የጽ/ቤት ሠራተኞች ፡ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተወካዮች፡ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል፡፡
የአሶሳ እንዚ መካነ ገነት መድኃኔአለም ካቴዴራል የህንፃ ግንባታ ኮሚቴ የመንበረ ጵጵስና ገዳማትና አድባራት የማጠናቀቂያ የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርጉለት ጠየቀ፤
ሀ/ስብከቱ የአሠሪ ኮሚቴውና የካቴዴራሉ ሰበካ ጉባኤ ያቀረበውን ጥያቄ መሠረት በማድረግ ከመንበረ ጵጵስና ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችና የሰበካ ጉባኤ አባላት ጋር ውይይት አድርጓል።
ለሦስት ቀናት የቆየው የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት 22ኛው መደበኛ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በሰላም ተጠናቀቀ።
ለሦስት ቀናት የቆየው የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት 22ኛው መደበኛ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በሰላም ተጠናቀቀ።
“ደን(ዕጽዋት )ለምድራችን የደም ሥርና ልብሷ ነው።ስለሆነም ምድራችን ስሯ ተቆርጦ ሕይወቷን እንዳታጣ የመጠቅና የመንከባከብ ኃላፊነት የሰው ልጆች በመሆኑ ደኖቻችንን በመንከባከብ ኃላፊነታችንን እንወጣ።”
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ “ሐዋርያዊ ተልእኳችን ለዘመናችን “በሚል ርእስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣በሰሜን አሜሪካ የኒዎርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ከጠቅላዮ ቤተ ክህነት ጀምሮ እስከ ክፍላተ ከተማ ለተውጣጡ የወንጌል መምህራን የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጠ።
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡