ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም (ልጅ ያሬድ) ማረሚያ ቤት እንዲወርድ ታዘዘ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም ባልቻ በቅጽል ስሙ (ልጅ ያሬድ) በቀረበበት ተደራራቢ ክስ ማረሚያ ቤት እንዲወርድ ታዘዘ።
“የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ከጠፋንበት አገኘችን” ትውልደ አሜሪካዊው ካህን
በዛሬው የሪፖርት ቀን ከሀገር ውስጥ አኅጉረ ስብከቶች በተጨማሪ ከኢትዮጵያ ውጭ ያሉ አኅጉረ ስብከቶች ሪፖርታቸውን ማቅረብ ጀምረዋል። በጉባኤው ላይ ከቀረቡት ሪፖርቶች መካከል አንዱ የሆነው የኒዮርክ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሪፖርት ሲሆን ያቀረቡት ትውልደ አሜሪካዊው መልአከ ገነት ተስፋ ኢየሱስ ናቸው።
በራያና አካባቢው የሚገኙ ስድስት ወረዳዎችን እንዲያስተባብር የተቋቋመው ጽሕፈት ቤት በ፵፪ኛው ዓለምአቀፍ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርቱን አቀረበ።
በሐምሌ ወር ፳፻ ፲ወ ፭ ዓ.ም አስቸኳይ ጉባኤውን ያካሄደው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በራያና አካባቢው ከሚገኙ ስድስት ወረዳዎች የቀረበለትን ጊዜያዊ ጽሕፈት ቤት ይቋቋምልንና የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ እንዲመሩን ይፈቀድልን በማለት ያቀረበውን ጥያቄ በመቀበል ችግሩ እስከሚፈታ ድረስ በአካባቢው የሚገኙ ምዕመናን አገልግሎት ማግኘት ይችሉ ዘንድ ጽሕፈት ቤቱ እንዲቋቋም ውሳኔ ማስተላለፉን ተከትሎ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤቱ ተቋቁሞ ፣ቢሮ ተከራይቶና ኃላፊዎች ተመድበውለት ሥራውን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱሳት መጻሕፍትን በአእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን የፈጠራ ባለቤትነት መብት ተመዘገበ።
የምዝገባ ሰርተፍኬት የተሰጠው ለስምንቱ ብሔረ ኦሪት ከዘፍጥረት እስከ መጽሐፈ ሩት ላለው ነጠላ ትርጉም መሆኑ ታውቋል።
ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማዕከል በ፵፪ ኛው አጠቃላይ ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤላይ ያቀረበው ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት የሚከተለው ነው።
ማኅበረ ቅዱሳን በ፳፻፲፭ ዓ.ም ካከናወናቸው መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶች ውስጥ የሚከተሉት ዐበይት ተግባራት ተጠቃሽ ናቸው፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት 42ኛ ዓመት የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ያስተላለፋት ሙሉ የመክፈቻ መልእክት
ጸዊረ መስቀል ምንም የመረረ ቢሆንም ተሸንፎ ግን አያውቅም ነገረ መስቀል በአሸናፊነት እንጂ በተሸናፊነት አይታወቅምና ነው ቅዱሳን ሐዋርያት ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ መግባት አለብን ሲሉ የመከራ መስቀል ዓጸፋ አሸናፊነትና መዳን መሆኑን ስለሚያውቁ ነው በሀገራችንም ሆነ በመላው ዓለም ዙሪያ ያሉ ክርስቲያኖች የተለያዩ ጸዋትወ መከራዎችን በመቀበል የሚገኙት ከመንፈስ ቅዱስ ኃይልና ከሐዋርያት ተጋድሎ ባገኙት ውርስ ነው፡፡
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በ፵፪ ኛው ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ የስተላለፉት መልዕክት።
ቅዱሳት መጻሕፍት በቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ሃይማኖታችን ላይ ስለሚመጣ ፈተና ዝግጁ ሆነን እንድንጠብቅቢያስ ገነዝቡንም ሊቁ አባታችን ቢንያሚን ደግሞ ለየት አድርጎ ‹‹ንኵን ድልዋነ ለሃይማኖት እንተ ኢትጸንን መጠርጠር ለሌለባት ሃይማኖትለሚመጣ ፈተና ዝግጁ እንሁን›› ብሎናል፡፡ በቤተ ክርስቲያን ሊመጣ የሚችልን ፈተና አስቀድሞ አውቆ የመውጫ መንገዱንም አዘጋጅቶ መጠበቅ የችግሩን መፍትሔ ግማሽ መንገድ እንደመራመድ ይቆጠራልና፡፡
የ፵፪ ኛው አጠቃላይ ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተጠናቀቀ።
፵፪ ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ነገ ጥቅምት ፭ ቀን ፳፻ ፲ወ ፮ ዓ.ም ይጀመራል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዶግማ፣ ቀኖና፣ ሕግና ደንብ የሚመራ “ፍኖተ ጽድቅ ብሮድካስት አገልግሎት” የተሰኘ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሊከፈት ነው።
ድርጅቱ የሚያቋቁመው ዘመናዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ የሚተዳደርበት ደንብና የሚዲያ ሥራውን የሚያከናውንበት ኤዲቶሪያል ፓሊሲ የቤተ ክርስቲያናችንን ዶግማ፣ቀኖና፣ሕግና መመሪያን መሠረት ያደረገ ሆኖ መዘጋጀት ይችል ዘንድ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት መምሪያ ኃላፊዎች፣ከሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፣ከታዋቂ ሰባኪያን፣ከታላላቅ የአገራችን የቴሌቪዥን ድርጅት የሥራ ኃላፊዎች የተውጣጣ ኮሚቴ እንዲቋቋም ተደርጓል።
ብፁዕ አቡነ ሄኖክ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የፍ/ደ/መዊዕ ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅ/አርሴማ ሰበካ ጉባኤ ጽሕፈት ቤትለሚያሳንጸው ሕንጻ ቤተክርስቲያን የመሰረት ድንጋይ አስቀመጡ።
ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል የበላይ ጠባቂ ሊቀ ጳጳስ እና ሊቀ ኅሩያን ዳዊት ታደሰ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ የፍ/ደ/መዊዕ ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት አርሴማ ሰበካ ጉባኤ ለሚያሳንጸው ሕንጻ ቤተክርስቲያን የመሰረት ድንጋይ አስቀመጡ።