የቦታው ስም ቀራንዮ ነው
የ2018 ዓ.ም. መስቀል በዓል ልዩ እትም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በሊቃውንት ጉባኤ ታይቶና ተመርምሮ፤ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተዘጋጀ
የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
በታላቁ ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የተፈፀመውን ጥቃት አስመልክቶ በምሥራቅ ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተመራ ውይይት ተካሄደ፡፡
የካቲት ፲፭ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
በ81 ዓመታቸው በድንገተኛ የመኪና አደጋ ያረፉት የሊቁ የመምህር ገብረ ዮሐንስ ገብረ ማርያም ሥርዓተ ቀብር ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በሚገኘው የበዓለወልድ ቤተክርስቲያን ተፈጸመ።
የካቲት ፲፪ ቀን ፲ወ፮ ዓ.ም
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ የዮርዳኖስ መንግሥት የቱሪዝም እና ጥንታዊ ቅርሶች ሚኒስትር ክቡር ማክራም ሙስጣፋ አብዱልከሪምን በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተቀብለው አነጋግረዋል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የካቲት ፲፫/፳፻፲፮ ዓ/ም የዮርዳኖስ መንግሥት የቱሪዝምና የጥንታውያት ቅርሶች ሚንስትር ክቡር ማክራም ሙስጠፋ አብዱልከሪምን በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተቀብለው አነጋግረዋል።
ሰሞኑን በማኅበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወረ ስለሚገኘው “መነኩሴ “ነኝ ባይ ግለስብ በሀገረ ስብከቱ የማይታወቅ መሆኑን ሀገረ ስብከቱ ገለጸ።
የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰሞኑን በማኅበራዊ ድረ ገጾች ራሱን “መነኩሴ”በማስመሰልና በአርሲ ሀገረ ስብከት አገልጋይ እንደሆነ በመግለጽ የሚንቀሳቀሰውን ግለሰብ የማያውቀውና ሐሰተኛ “መነኩሴ” መሆኑን ለጠቅላይ ቤተክህነት በጻፈው ደብዳቤ አስታወቀ።
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተላለፈ ወቅታዊ መልዕክት።
ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም:- የካቲት 12 ቀን በታጣቂ ቡድኖች ከተወሰዱ በኋላ አራቱም በትላንትናው አለት የተገደሉ ሲሆን አባ ኪዳነማርያም ገ/ሰንበት የተባሉት አባት ቆስለው በገዳሙ እንደሚገኙ ታውቋል።
በኦስሎ ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምርህታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ደቀመዛሙርት ማዕርገ ዲቁና ተቀበሉ።
በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ኤልያስ መልካም ፈቃድ አሳሳቢነት የአብነት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ለቆዩት አራት ደቀ መዛሙርት የዲቁና ሥልጣነ ክህነት በሰጡበት ወቅት ለአገልጋዮቹ በሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ትምህርት አስተምረው በዓለም ዙሪያ ያለችውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን በቅንነትና በእውቀት እንዲያገለግሏትም አባታዊ መመሪያም አስተላልፈዋል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ የካቲት 11/06/2016 ዓ/ም ለሰባት ማኅበራት የዕውቅና ሰርተ ፍኬት ሰጠ።
የተሰጣቸው ሰርተፍኬት ለሦስት ተከታታይ ዓመታት ይቆያል ተብሏል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የማኅበረ ቅዱሳን አመራሮችን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ።
የካቲት ፭ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር እና ሰሜን ጎጃም አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰዋሰወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሥራ ጉብኝት አደረጉ።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር እና ሰሜን ጎጃም አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰዋሰወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ አስተዳደር እና ደቀመዛሙርትን በመጎብኘት አባታዊ ቡራኬ እና የሥራ መመሪያን አስተላልፈዋል፡፡
የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻና ግብረ ሰዶማዊነትን አስመልከቶ እየተደረጉ ያሉ ሁለገብ ተጽእኖዎችንና መመሪያ የማስለወጥ ማግባባቶችን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡
የካቲት ፬ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም