ልማት በቤተ ክርስቲያን
ልዮ ዕትም መጽሔት
ይህ ”ልማት በቤተክርስቲያን“ የተሰኘ ልዮ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
የመስቀል ደመራ በዓል የአከባበር ሥነ ሥርዓት ዝግጅት ተጠናቀቀ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓት ከምታከብራቸው የአደባባይ በዓላት መካከል አንዱና በዓለም አቀፉ የትምህርት ሳይንስና ባህል ጅርጅት በማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበው የመስቀል ደመራ በዓል በነገው ዕለት በመስቀል አደባባይ በታላቅ ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓት ይከበራል ።
ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና ብፁዕ ዶክተር የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የ2016 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል አስመልክቶ የሊቃውንት ወረብ ጥናት ልምምድን ጎበኙ።
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር ከሚገኙ ገዳማትና አድባራት የተውጣጡ ብዛታቸው 800 የሚደርሱ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በ2016 ዓ.ም የሚከበረውን የመስቀል ደመራ በዓል በተለየ ድምቀት ለማክበር ከነሐሴ 24 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በጠቅላይ ቤተ ክህነትና በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ግቢ በዓሉን የተመለከተ የወረብ ጥናት ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆን መስከረም 14 ቀን 2016 ዓ/ም በተደረገው የወረብ ጥናት መርሐ ግብር ወቅት ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተገኝተው ለሠልጣኞቹ የማበረታቻ ሐሳብና ቡራኬ ሰጥተዋል።
ዓለም በሚቀማበት ወቅት ጊዜውን፣እውቀቱን፣ገንዘቡን ለቤተ ክርስቲያን የሚሰጥ እንደእናንተ አይነት ልጆች ስላሉን እግዚአብሔርን እናመሰግነዋለን
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በማኅበረ ቅዱሳን የ2016 ዓ.ም የ6 ወራት የሥራ አመራር ጠቅላላ ጉባኤ ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው ቡራኬና ቃለ ምእዳን ሰጥተዋል።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመስቀል አደባባይ የሚከበረውን የደመራ በዓልን አስመልክቶ መልእክት አስተላለፉ።
ብፁዕነታቸው በመግቢያቸው ስለ ትግስት አስፈላጊነት እና ጠቀሜታ ትምህርት የሰጡ ሲሆን በበዓሉ ላይ የሚፈትኑ ጉዳዮች ሊገጥሙን ስለሚችሉ በትዕግስት ማለፍ አለብን ብለዋለል። በማስከተልም የዕለቱን መርሐ ግብር ያስተዋወቁ ሲሆን በይበልጥም ሰዓትን ማክበር ከፍተኛ ትኩረት እንደሚሰጠው አሳስበዋል። ብፁዕነታቸው የመግቢያ ባጅ እደላው በሕግና በሥርዓት ትኩረት ተሰጥቶት የሚከናወን መሆኑን ገልጸዋል።
በመቅደላ ጦርነት ወቅት በእንግሊዝ ወታደሮች ከተዘረፉ የብራና መጻሕፍትና ልዩ ልዩ ንዋየ ቅድሳት መካከል እንደሆነ የሚገመት አንድ ጽላት እና የተለያዩ ቅርሶች በበጐ አድራጊዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ የርክክብ ሥነ ሥርዓት በታላቋ ብሪታንያ ለንደን ከተማ ተከናወነ።
በዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ለንደን (UCL) መምህር የሆኑትና ለረጅም ጊዜ በኢትዮጵያና በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤክርስቲያን ጉዳይ ላይ ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር ጃኮፖ ግኒስኪ በመቅደላ ጦርነት ዘመን ከአገር እንደወጣ የሚገመትና በእርሳቸው እጅ የነበረ ጽላት ወደ ሀገሩና ወደ መንበረ ክብሩ እንዲመለስ ከፍተኛውን አስተዋጽዖ እንዳበረከቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን በመወከል ጽላቱን የተረከቡት የልዑካን ቡድኑ ተወካይ ቀሲስ ዶ/ር አባተ ጐበና ምስጋናቸውን በልዑካኑ ስም ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።
ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል በዶምቢዶሎ ሎና በቄለም ወለጋ ልዩልዩ የልማት ሥራዎችን አከናወኑ ለችግረኛ ተማሪዎችም የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አየረጉ።
ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል የጋምቤላ፣የአስሳ፣የቄለም ወለጋና የደቡብ ሱዳን አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በደምቢዶሎ ከተማ በሚያደርጉት ሐዋርያዊ አገልግሎት በደምቢዶሎ ከተማ ቀበሌ03 በአርባ ቀናት ተሰርቶ የተጠናቀቀውን የቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን መስከረም 6ቀን 2016ዓ.ም ቅዳሴ ቤቱን ማክበራቸውን የሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤት ሕዝብ ግንኙነት ክፍል በላከልን ዘገባ ገልጿል።
የጥቅምት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ጥሪ ተላለፈ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዓመት ሁለት ጊዜ ከሚያደርጋቸው የምልአተ ጉባኤ ስብሰባዎች አንዱ የሆነው የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ መሆኑ ይታወቃል። የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የዘንድሮው የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ ከጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፲፮ ዓ/ም ጀምሮ እንደሚካሄድ በመግለጽ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና ጳጳሳት ጥቅምት ፲፩ ቀን ፳፻፲፮ ዓ/ም በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ እንዲገኙ መንፈሳዊ ጥሪውን አስተላልፏል።
በውጭ አገር ለምትገኙ አህጉረ ስብከት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተላለፈ መልዕክት
ለሁለተኛ ጊዜ በውጭ አገር ለሚገኙ አህጉረ ስብከት ጥሪ ተላልፏል።ስለሆነም በተላለፈው ጥሪ መሰረት ዝርዝራችሁ ከዚህ ደብዳቤ ጋር የተለጠፈው አህጉረ ስብከት በአስቸኳይ ሪፖርታችሁን እንድታቀርቡና በገጉባኤው ላይ እንድትሳተፉ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን ።
የመስቀል ደመራ በዓል የቅድመ ዝግጅት ሥራ በአምስት ማዕከላት በመከናወን ላይ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል የቅድመ ዝግጅት ሥራውን እያከናወነ ነው።
በዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የደረሰውን ዝርፊያ በተመለከተ አሰፈላጊው ክትትል እየተደረገ ነው።
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሚገኘው የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም በትላንትናው እለት ማንነታቸው ባልታወቁ ዘራፊዎች የደረሰበትን ዝርፊያ በተመለከተ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስፈላጊውን ክትትልና ማጣራት በማድረግ ላይ የምትገኝ ሲሆን በጉዳዩ ዙሪያም ከሚመለከታቸው የመንግሥት የጸጥታ አካላት ጋር እየተነጋገረችበት ነው።