የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የብፁዕ አቡነ ሰላማ አጭር የሕይወት ታሪክ

September 29, 2023

ዜና ህይወቱ ለብፁዕ አቡነ ሰላማ (የብፁዕ አቡነ ሰላማ አጭር የሕይወት ታሪክ)

ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከአባታቸው ከአቶ ገብረ ሥላሴ ገ/መድኀንና ከእናታቸው ከወ/ሮ ብዙነሽ ወንድሙ በትግራይ ክፍለ ሀገር በመቀሌ ከተማ ልዩ ስሙ በዓታ ለማርያም በተባለው ፲፱፴፬ ዓ/ም ተወለዱ።

ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በትውልድ ሀገራቸው ንባብና የቃል ትምህርት በሚገባ የተማሩ ሲሆን ለግብረ ዲቁና የሚገባውንም ትምህርት ከየኔታ ክነፈ
ርግብ ተምረዋል ፤ ዲቁና ከብፁዕ አቡነ ማርቆስ ተቀብለዋል።
ብፁዕነታቸው ለቤተክርስቲያንና ለመንፈሳዊ ዕውቀት ባላቸው ጥልቅ ፍቅር በተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር የተለያዩ መንፈሳዊ ትምህርቶችን የተማሩ ሲሆን

ዜማ፡- ከየኔታ ተክለ ማርቆስ ማየ አንበሳ ገዳም (ተንቤን)
– ቅኔ፡- ከየኔታ ንጉሤ መነዌ ገዳም (ተንቤን)

– ቅኔ፡- ከየኔታ አክሊሉ ደበጋ (ጐንደር)
• ትርጓሜ መጻሕፍት- ከየኔታ ኃ/ማርያም ቀረፃ ማርያም ከምትሀባል ገዳም
ቅኔና ትርጓሜ መጻሕፍት፡- እንድባ ጊዮርጊስ ከየኔታ ልሳነ ወርቅ (ጐጃም)
● ቅኔ፡- ከየኔታ ዲበኩሉ (ጐጃም) በሚገባ ከተማሩ በኋላ ለመምህር ነት በቅተዋል፡፡
ከዚህ በኋላ በጐጃም ክ/ሀገር በፈረስ ቤት ሚካኤል፣ በጅጋ ሚካ ኤል ወንበር ዘርግተው ለ፲፪ ዓመታት ቅኔ በማስተማር አያሌ ደቀ መዛሙርትን አፍርተዋል፡

መዝገበ ቅዳሴ ከየኔታ ልዑል (ቦረራ ሚካኤል) ተምረዋል፤ በወ ቅቱ የጐጃም ሊቀ ጳጳስ ከነበሩት ከብፁዕ አሱነ ማርቆስ የቅስናና የምንኵስና መዐርግ ተቀብለዋል።

ብፁዕ አቡነ ሰላማ በ ፲፱፻፷፬ ዓ.ም ወደ አርሲ ክፍለ ሀገር በመሄድ በወቅቱ የሀ/ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በነበሩት በብፁዕ አቡነ ሉቃስ መልካም ፈቃድ በሀገረ ስብከቱ በማስተማር፣ የአውራጃ ሰባኬ ወንጌል በመሆን፣ የወረዳ ሊቀ ካህናት በመ ሆን በተለያዩ የኃላፊነት ሥራዎች ተመድበው በመሥራት ሰፊ አገልግሎት አበርክተዋል፤ በርካታ ደቀ መዛሙርትንም አፍርተዋል፤ በዚሁ ሀገረ ስብከት ለ፳፪ ዓመታት በማስተማር ቆይተዋል፤ በዚህም ሰፊ ወቅት ብዙ ደቀ መዛሙርትን አውጥተው ለቤተ ክርስቲያን አበርክተዋል፡፡

ብፁዕነታቸው ከአርሲ ሀገረ ስብከት በ፲፱፻፹፮ ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ ከመጡ በኋላ ውቅያኖስ በሆነው እውቀታቸውና በቅድስናቸው ቤተ ክርስቲያንንም ሆነ ምእመናንን እንደሚጠቅሙ በማሰብ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት በቅዱሳን ፓትርያርኮች ፈቃድና ትእዛዝ እየተሾሙ፦-
⇨ በቡራዩ ፄዴንያ ማርያም፣
⇨ በመተሐራ መድኃኔ ዓለም፣
-በቃሊቲ ቅዱስ ገብርኤልና ሳሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣
⇨ በሰዓሊተ ምሕረት፣
⇨ በደብረ አሚን ተክለ ሃይማኖት በአስተዳዳሪነት ተመድበው ለበር ካታ ዓመታት በማስተማር በሚያስመንነው ስብከታቸው ብዙ አማ ንያንን አበርክተዋል፤ ለምናኔም አብቅተዋል፤ በተሰጣቸው ሀብተ ፈውስ በጸሎታቸው አያሌ ሕሙማንን ፈውሰዋል፧ ሰበካ ጉባኤን አጠናክረዋልº ስብከተ ወንጌልን አስፋፍተዋል፧ በተለይም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሊቀ ሥልጣናት ሆነው ለ ዓመታት ያህል በአስተዳደሩበት ጊዜ ከፈጸሟቸው ተግባራት ዋና ዋናዎቹ ምእመናን በጣዕመ ስብከታቸውና በቅድስናቸው እየተማረኩ ለካቴድራሉ በሚያደርጉት የቦታና የገንዘብ ልግስና በርካታ የሆኑ የልማት ተግባራትን አከናውነዋል።

❖ በዚህም መሠረት በትምህርታቸው በጎ አድራጊዎችንና ምእመናንን በማስተባበር በካቴድራሉ ስም የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤትና ከፍተኛ ክሊኒክ አሠርተው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ሊቀ ጳጳስ አክ ሱም፣ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ተባርኮ አገልግሎት በመስጠት ላይ ነው፡፡

⇨ በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለ፭ ዓመታት ካገለገሉ በኋላ በእን ጦጦ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ገዳም በአስተዳዳሪነት አገልግለዋል።

⇨ ብፁዕ አቡነ ሰላማ ሙሉ የቤተ ክርስቲያን ትምህርታቸውን አጠናቅቀው በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ከተመደቡበት ጊዜ ጀምሮ ከቦታ ወደ ቦታ በመዘዋወር በአብነት መምህርነታቸው በተለይም በቅኔ መምህርነታቸው በተለያዩ አህጉረ ስብከት ወንበር ዘርግተው በማስተማር እስከ ጵጵስና ደረጃ የደረሱ አያሌ ምሁራንን አፍርተው ለቤተ ክርስቲያን ያስረከቡ፣ በልዩ የስብከት ችሎታቸው የታወቁ ሰባክያነ ወንጌልን ያፈሩና አማንያንን ያበዙ፣ ቅድስናን ከሙያ ጋር አስተባብረው የያዙ፣ የቅዱሳኑ፣ የፍጹማኑ ረድኤት ያልተለያቸው፣ እንደ አባቶቻቸው ቅዱሳን ሐዋር ያት አጋንንትን የማስወጣትና ሌላውንም ደዌ ሁሉ የመፈወስ ሀብተ ፈውስ የተሰጣቸው፣ በጥላቸው ብቻ ሕሙማንን የሚፈ ውሱ፣ የበቁ (ፍጹም) አባት ነበሩ።

ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከፈጣሪያቸው የተሰጣቸው ተውህቦ የተወሰነ አይደለም ሀብተ ጸጋቸው ብዙ ነው! ጣዕመ ስብከታቸው ካለ መጠገቡም በላይ በተመስጦ በአካለ ሥጋ ያሳርጋልI ቅኔያቸውም ልዩ ጣዕም አለው ከማር ከወተት ይጣ ፍጣል! ፈጣሪያቸውን ብቻ አይደ ለም የሚያከብሩት፣ ሲበዛ ሰው አክባሪ ናቸው‥ ምንም ይሁን ምን በአርአያ እግዚአብሔር የተፈጠረውን ትልቁንም ትንሹንም ሁሉ በአክብሮት የሚወዱ አባት ነበሩ።

በአጠቃላይ ብፁዕ አቡነ ሰላማ የቤተ ክርስቲያናችን ጸጋና በረከት ነበሩ።በዚህ ቅድስና ቸው፣ በቤተ ክርስቲያን ትምህርት ሙሉ ችሎታቸው፣ በአብነት መምህርነታቸው በርካታ ምሁራንን በማፍራታቸውና ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናቸው ባበረከቱት ሰፊ የሆነ መንፈሳዊ አገልግሎታቸው ተመዝነው ብቁና ፍጹም አባት ሆነው በመገኘታቸው ሐምሌ ፱ ቀን ፲፱፻፺፯ ዓ.ም በተደረገው የጳጳሳት ምርጫ ከሌሎች ዕጩ ቆሞሳት ጋር ተወዳድረው የድምፅ ብልጫ ስለ አገኙ የአክሱምና ማዕከላዊ ዞን ሃገረ ስብከት ኤጲስ ቆጶስ ሆነው የተመደቡ ሲሆን ከታኅሣሥ ፱/ ፪ሺ፪ ዓ/ም ጀምሮ የሰሜን ምዕራብ ሽሬ እንዳሥላሴ ሀገረ ስብከትን ደርበው እየሰሩ እስከ ግንቦት ፳፰/፪ሺ፭ ዓ/ም ድረስ ሐዋርያዊ ተግባራቸውን ሲፈጽሙ ቆይተዋል።

ግንቦት ፳፰ /፪ሺ፭ ዓ/ም ከትግራይ ማዕከላዊ ዞን አክሱም ሀገረ ስብከት ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተዛውረው የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም እና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የበላይ ኃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተው በ ፪ሺ፮ ዓ/ም የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመሆን ለ፮ ዓመታት በምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ከፍተኛ ሐዋርያዊ አገልግሎትን ፈጽመዋል።

ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከህዳር ፳፻ ፲፪ዓ/ም ጀምሮ በድጋሚ የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም እና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የበላይ ኃላፊ ሆነው በበአታቸው በመወሰን ሲያገለግሉ ቆይተው ባደረባቸው ሕመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው መስከረም ፲፰ቀን፳፻ ፲ወ፮ ዓ/ም ይህን ዓለም በዕረፍተ ሥጋ ተለይተው ወደ ሰማያዊው አባታቸው ተጉዘዋል።

በረከታቸው ይደርብን

የብፁዕነታቸው በረከት ይደርብን

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/photo_2023-09-29_17-42-09-cover.jpg 402 400 tc https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg tc2023-09-29 15:45:022023-09-29 15:45:02የብፁዕ አቡነ ሰላማ አጭር የሕይወት ታሪክ
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ዜና እረፍት – ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ። Link to: ዜና እረፍት – ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ። ዜና እረፍት – ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከዚህ ዓለም... Link to: ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የብፁዕ አቡነ ሰላማ የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም እና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የበላይ ጠባቂ ሊቀጳጳስ ዕረፍትን በማስመልከት ያስተላለፉት አባታዊ የሐዘን መግለጫ Link to: ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የብፁዕ አቡነ ሰላማ የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም እና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የበላይ ጠባቂ ሊቀጳጳስ ዕረፍትን በማስመልከት ያስተላለፉት አባታዊ የሐዘን መግለጫ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top