የቦታው ስም ቀራንዮ ነው
የ2018 ዓ.ም. መስቀል በዓል ልዩ እትም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በሊቃውንት ጉባኤ ታይቶና ተመርምሮ፤ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተዘጋጀ
የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
የመስቀል ደመራ በዓል የቅድመ ዝግጅት ሥራ በአምስት ማዕከላት በመከናወን ላይ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል የቅድመ ዝግጅት ሥራውን እያከናወነ ነው።
በዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የደረሰውን ዝርፊያ በተመለከተ አሰፈላጊው ክትትል እየተደረገ ነው።
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት የሚገኘው የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም በትላንትናው እለት ማንነታቸው ባልታወቁ ዘራፊዎች የደረሰበትን ዝርፊያ በተመለከተ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስፈላጊውን ክትትልና ማጣራት በማድረግ ላይ የምትገኝ ሲሆን በጉዳዩ ዙሪያም ከሚመለከታቸው የመንግሥት የጸጥታ አካላት ጋር እየተነጋገረችበት ነው።
የቅድስት ልደታ ጤና ኮሌጅ በተከታታይ ዓመታት ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ።
የቅድስት ልደታ ጤና ኮሌጅ በተከታታይ ዓመታት ያስተማራቸውን ተማሪዎች ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ በተገኙበት አስመረቀ።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የ፳፻ ፲ወ፮ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል አከባበር የዝግጅት ሥራ ግምገማ ተካሔደ ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በ፳፻፲፭ ዓ/ም የሥራ ዓመት በነበረው የሥራና የአገልግሎት አፈጻጸም ዙሪያ አጠቃላይ የጠቅላይ ጽ/ቤቱ ሠራተኞች በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አሥኪያጁ በብፁዕ አቡነ አብርሃም መሪነት በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ሠፊ ውይይት አደረጉ።
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤ ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዓውደ ዓመት ዘዕስራ ምእት ዐሠርቱ ወስድስቱ ዓመተ ምሕረት
አዲሱ ዓመት የሰላምና የፍቅር፣ የዕርቅና የይቅርታ የተፈናቀለው ወደቀየው የሚመለስበት፣ ሆድ የባሰው የሚጽናናበት፣ ፍትሕና ርትዕ የሚሰፍንበት የመሳሪያ ድምፅ የማይሰማበት ፍጹም የተግባቦት ዓመት እንዲሆንልን እየጸለይን ሁሉም ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን ለዚህ ቅዱስ ጥሪ አዎንታዊ መልስ እንድትሰጡ አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም በድጋሚ እናስተላልፋለን፡፡
የመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በ ፳፻፲፭ ዓ/ም አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት አካሄዱ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በ፳፻፲፭ ዓ/ም የሥራ ዓመት በነበረው የሥራና የአገልግሎት አፈጻጸም ዙሪያ አጠቃላይ የጠቅላይ ጽ/ቤቱ ሠራተኞች በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አሥኪያጁ በብፁዕ አቡነ አብርሃም መሪነት በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ሠፊ ውይይት አደረጉ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልጅ ያሬድ በተባለው ግለሰብ እና ተባባሪዎቹ ላይ ክስ እንዲመሠረት ለፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ ጥያቄ አቀረበች።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልጅ ያሬድ በተባለውን ግለሰብ እና በተባባሪዎቹ ላይ ክስ እንዲመሠረት ለፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ቢሮ በላከችው ደብዳቤ ጠይቃለች።
“ቤተክርስቲያን የተፈተነችበት ሥርዓቷን እና ልጆችዋን ያጣችበት ጊዜ ስለሆነ ለሀገራችን እና ለቤተ ክርስቲያናችን ሰላም እንዲመጣ የጷጉሜን ፮ቀናት ወደ እግዚአብሔር እንጸልይ።” ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የጷጉሜን ፮ ቀናት ጸሎተ ምህላ እንዲኖር አወጀ።
ልጅ ያሬድ የተባለውን ግለሰብ በህግ ለመጠየቅ የሚያስችል ሥራ እየተሰራ ነው።
ነሐሴ ፳፮ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን የ፲ ዓመት መሪ እቅድ ሥልጠና በብፁዕ ቅዱስ ፓትርያርኩ ቃለ በረከት ተከፈተ::
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በመሪ እቅድ መምሪያ ያዘጋጀው የ፲ ዓመት መንፈሳዊና ዘላቂ የልማት ግቦች ጉባኤ በእግዚአብሔር ኃይል ጠንካራና ሁለገብ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብን ለመገንባት እንተጋለን ! በሚል ርዕስ ለአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችና ምክትል ሊቃነ መናብርት በተገኙበት በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ሁለገብ አዳራሽ ዛሬ ሐሙስ ነሐሴ ፳፭ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም. ከጠዋቱ ፫ ሰዓት ጀምሮ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ውይይትና ምክክር እየተከናወነ ነው፡፡