ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
አዲስ ለሚሾሙት ኤጲስ ቆጶሳት የጸሎተ አስኬማ ሥነሥርዓት ተከናወነ።
በዛሬው ዕለት በተፈጸመው ጸሎተ አስኬማ ለሥርዓቱ የተሠራው ጸሎት በቅዱስነታቸው መሪነት ከደረሰ በኋላ ቡራኬ የተሰጠበትን ቅናተ ዮሐንስ ቅዱስነታቸው ለተሿሚ ቆሞሳት አስታጥቀዋል።
የኮሎራዶና አካባቢው ሀገረ ስብከት አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በዛሬው ዕለት መካሔድ ጀመረ።
በሰሜን አሜሪካን የኮሎራዶና አካባቢው ሀገረ ስብከት አምስተኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዛሬ ሐምሌ ፯ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም በኦምሐ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን መካሔድ ጀመረ።
ቅዱስ ሲኖዶስ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲያደርግ የነበረውን አስቸኳይ ጉባኤ በማጠናቀቅ መግለጫ ሰጠ።
በክልል ትግራይ በተካሄደው ጦርነት በቤተ ክርስቲያናችን የበላይ መዋቅርና በክልል ትግራይ አህጉረ ስብከት መካከል የነበረው አስተዳደራዊ መዋቅር ተቋርጦ መቆየቱን ተከትሎ የተፈጠረው አለመግባባት በውይይት ተፈቶ መዋቅራዊ አንድነታችን በድጋሚ ተጠናክሮ እንዲቀጠል ሀገራዊ የሰላም እርቁ ከተፈጸመበት ማግስት ጀምሮ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ፊርማ በተደጋጋሚ በደብዳቤ ሲጠየቅ መቆየቱ ይታወሳል፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልአተ ጉባኤ ተጠራ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ እና በአዲስ አበባ አቅራቢያ ያሉ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ለዛሬ ሐምሌ ፭ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት በቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ ለአስቸኳይ የምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ እንዲገኙ ጥሪውን አስተላልፏል።
ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁን በተመለከተ በትግራይ ተፈናቃዮች የተደረገው መሰረተ ቢስ ውንጀላ ፍፁም ከእውነት የራቀ ነው።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም ወደ አሥመራ ተጉዘው ከፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ጋር የተገናኙት ሁሉም ኢትዮጵያዊ በኤርትራና በኢትዩጵያ ስምምነት በተደሰተበት ማግስት የተፈጠረውን ሰላምና ዕርቅ እውቅና ለመስጠት በተደረገ ሥነሥርዓት ላይ ለመገኘት የአማራ ክልል ልዑክ በመሆን መጓዛቸው በቀጥታም ህነ በተዘዋዋሪ ከትግራይ ጦርነት ጋር ግንኙነት የለውም።
ቅዱስነታቸው በትግራይ የሚገኙ አባቶች ችግሩን በጠረጴዛ ዙሪያ በሚደረግ ውይይት እንዲፈቱ ጥሪ አቀረቡ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በክልል ትግራይ በጦርነቱ ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች ርዳታ ለመስጠትና በትግራይ ከሚገኙ አባቶች ጋር የተፈጠረው ችግር በውይይት ለመፍታት ዛሬ ፣ ሐምሌ ፫ቀን ፳፻ ፲ወ፭ዓ.ም ማለዳ መቐለ ከተማ ገብተዋል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለትግራይ ክልል የ20 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገች
(ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለትግራይ ክልል የ፳ ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገች፡፡በድጋፍ ርክክብ መርሐ ግብሩ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ፣ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት እና ልዑካን ቡድኑ ተገኝተዋል፡፡
በቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ ልዑካን ቡድን ወደ ክልል ትግራይ ርዕሰ ከተማ መቐለ ተጓዘ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ለክልል ትግራይ የሰብዐዊ ድጋፍ እንዲደረግና ቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በትግራይ ክልል ከሚገኙ አባቶች ጋር ውይይት እንዲደረጉ ውሳኔ አስተላልፏል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የማኅበራት ምዝገባና ክትትል መምሪያ ቀጣዩን የሥራ አተገባበር አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያ የማኅበራት ምዝገባና ክትትል መምሪያ በጥቅምት ወር ፳፻፲፭ ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ ዕውቅና ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ የውስጥ አሠራሩን ሲያመቻች የቆየ መሆኑን የሕግ ባለሙያው አቶ አያሌው ቢታኒ ሐምሌ ፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ተናግረዋል።
ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ደቀመዛሙርትን አስመረቀ
ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ በሥሩ ባሉ የተለያዩ ኮሌጆችና በተለያዩ የትምህርት ክፍሎች በመደበኛ፣ በተከታታይ፣ በርቀትና በልዩ የካህናት ሥልጠና ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ፫፻፸፮ ደቀመዛሙርትን በድኅረ ምረቃ፣ በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በዲፕሎማና በሰርተፊኬት ማዕረግ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒው ዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የዩኒቨርሲቲው የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ፣ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳት፣ ክቡር ሊቀ አእላፍ በላይ መኮንን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ እንዲሁም በክብር ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የተመራቂ ቤተሰቦች በተገኙበት በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስመረቀ።