የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የ፳፻ ፲ወ፮ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል አከባበር የዝግጅት ሥራ ግምገማ ተካሔደ ።

September 15, 2023

መስከረም ፬ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ዓ.ም
“””””””””””””””””””””””””””””””
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
******
በየዓመቱ መስከረም ፲፮ ቀን በታላቅ ሃይማኖታዊ ሥነሥርዓት የሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል በአገር አቀፍ ደረጃ በመስቀል አደባባይ ቅዱስ ፓትርያርኩ ፣ብፁዐን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣የመንግስት ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣የከተማችን አስተዳደር ከንቲባ፣
አምባሳደሮች፣ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች፣
ካህናት፣የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች በብዙ ሺህዎች የሚቆጠሩ ምዕመናንና ምዕመናት በተገኙበት እንደሚከበር ይታወቃል።

በዓሉ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ በድምቀት ተከብሮ ይውል ዘንድም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ዐቢይና ንዑሳን ኮሚቴዎችን በማደራጀት በርካታ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን ስታከናውን ቆይታለች።

የዐቢይ ኮሚቴ አባላቱም በስራቸው የተደራጁ ንዑሳን ኮሚቴዎችን በማስተባበርና ተለይቶ የተሰጣቸውን ሥራዎች በማከናወን ለዐቢይ ኮሚቴው በሪፖርት ሲያሳውቁና የተግባራቶቻቸውን አፈጻጸም መሰረት ያደረገ ሥራ ሲያከናውኑ ቆይተዋል።በተለይም በቀጥታ ከበዓል አከባበሩ ጋር የተያያዙ ሥራዎችን የሚያከናውኑ ማለትም የካህናት ፣የሰንበት ትምህርት ቤት፣የሥነ ጽሑፍ፣የደመራ ዝግጅት፣ የእስቴጅ ዝግጅትና የባጅ ዝግጅት ንዑሳን ኮሚቴዎች አስፈላጊውን ሥራ ሁሉ ቀድመው ማከናወናቸውን መነሻ ያደረገ የእቅድ ክንውን ግምገማ በዛሬው ዕለት በጠቅላይ ቤተክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ተከናውኗል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንዲሁም የዐቢይ ኮሚቴው ሰብሳቢ ብፁዕ አቡነ አብርሃምና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒዩወርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዶ/ር ተገኝተዋል።

በእቅድ አፈጻጸም ግምገማው ላይ በዓሉን በድምቀትና ሰላማዊ በሆነ መልኩ ለማክበር ይቻል ዘንድ አስቀድሞ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።በቀሪ ቀናት የሚከናወኑ ሥራዎችም በፍጥነትና ሕግና መመሪያን በጠበቀ አግባብ እንዲከናወኑም በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አቅጣጫ ተቀምጧል።

በእቅድ አፈጻጸም ግምገማው ላይ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ እንደገለጹት በዓሉ ሃይማኖታዊና አገር አቀፋዊ መሆኑን መሰረት ያደረገ ሥራ መከናወን እንደሚገባው ጠቁመው በዓላችን ዓለም አቀፋዊ እውቅና ያለውና ለአገራችን ገጽታ ግንባታም ጉልህ ድርሻ የሚያበረክት መሆኑን አስታውሰው የበዓል አከባበሩ ሂደት ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን የጠበቀና ፍጹም ሰላማዊ መሆን ይችል ዘንድ ከዐቢይ ኮሚቴው ጀምሮ በየደረጃው የሚገኙ የቤተክርስቲያናችን የሥራ ኃላፊዎች በትጋት መስራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል ።

ወጣት የቤተክርስቲያን ልጆችም ከማዕከላዊ የቤተክርስቲያናችን አስተዳደር የሚሰጡ መመሪያዎችን በማክበርና መርሐ ግብሩ በተያዘለት ዕቅቅ መሰረት መከናወን ይችል ዘንድ የሚጠበቅባቸውን ሃይማኖታዊ አክተዋጽኦ በፍጹም ክርስቲያናዊ ጨዋነት ማበርከት ይኖርባቸዋል ብለዋል።

በዓላችን በደመቀ መልኩ ያለ አንዳች የጸጥታ ችግር ተከብሮ መዋል ይችል ዘንድም ሁላችንም ሕግ አስከባሪ፣ሁላችንም ጸጥታ አስከባሪና አስተባባሪ በመሆን ከመስራት ጀምሮ የመንግስት የጸጥታ አካላት ሰላምና ጸጥታን ለማስከበር የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ በቀና መንፈስ በመደገፍ በዓላችን ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላም እንዲከበር ማድረግ ይኖርብናል ካሉ በኋላ በመንግስት የጸጥታ አካላት የማይፈቀዱ ማናቸውንም ተግባራት ባለመፈጸምም ሕግ አክባሪነታችንን በተግባር ማሳየት ይኖርብናል ብለዋል።

በመርሐ ግብር አተገባበር ዙሪያ በየጊዜው የሚስተዋሉ መጓተቶች አግብብ አለመሆናቸውን የጠቆሙት ብፁዕነታቸው ያስቀመጥነውን የጊዜ መርሐ ግብር ማክበርና ማስከበር ከሁላችንም የሚጠበቅ መሆኑን በመገንዘብ ለተግባራዊነቱ የጋራ ጥረት ማድረግ እንደሚገባ ጨምረው ገልጸዋል።

የዘንድሮ የመስቀል ደመራ በዓላችን ሙስሊም ወገኖቻችን የመውሊድ በዓልን ከሚያከብሩበት ቀን ጋር የተገጣጠመ በመሆኑ በዓላችንን ፍጹም ሰላማዊ በሆነና የቀደመ መከባበርና መቻቻላችንን መሰረት ባደረገ አግብብ በፍቅር ማክበር ይኖርብናል ያሉት ብፁዕነታቸው የበዓል አከባበር ሒደቱን በማስመልከትም በቤተክርስቲያናችን የመገናኛ ብዙሃን አማካኝነት ከወዲሁ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐ ግብሮች እንዲከናወኑ ይደረጋል ብለዋል።በማያያዝም ሁሉም የበዓሉ ታዳሚና በበዓሉ ላይ ትርኢት የሚያቀርቡ አካላት ሁሉ የቤተክርስቲያናችንን አርማ ብቻ ሊጠቀሙ ይገባል ብለዋል።

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዶ/ር በበኩላቸው በዓላችን ፍጹም ሃይማኖታዊ በመሆኑ ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ አግባብ ብቻ እንዲከበር ማድረግ እንደሚያስፈልግ ገልጸው ስለበዓላችን አጠቃላይ እንቅስቃሴና የአከባበር ሂደት የቤተክርስቲያናችን ሚዲያዎች አስቀድመው ዝርዝር ማብራሪያዎችና የግንዛቤ ማሳደጊያ መልዕክቶችን ማስተላለፍ እንደሚገባቸው ገልጸዋል።

Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤ ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዓውደ ዓመት ዘዕስራ ምእት ዐሠርቱ ወስድስቱ ዓመተ ምሕረት Link to: ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤ ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዓውደ ዓመት ዘዕስራ ምእት ዐሠርቱ ወስድስቱ ዓመተ ምሕረት ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ... Link to: የቅድስት ልደታ ጤና ኮሌጅ በተከታታይ ዓመታት ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ። Link to: የቅድስት ልደታ ጤና ኮሌጅ በተከታታይ ዓመታት ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ። የቅድስት ልደታ ጤና ኮሌጅ በተከታታይ ዓመታት ያስተማራቸውን...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top