የቦታው ስም ቀራንዮ ነው
የ2018 ዓ.ም. መስቀል በዓል ልዩ እትም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በሊቃውንት ጉባኤ ታይቶና ተመርምሮ፤ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተዘጋጀ
የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
በሰሜን አሜሪካ ተተኪ ካህናትን በበቂ ሁኔታ የማፍራት ሂደት ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) ገለጹ።
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰሜን አሜሪካን በሲራኪዮስ ከተማ በምትገኘው የገነተ ደናግል ቅድስት አርሴማ ወክርስቶስ ሰምራ ገዳም ተገኝተው በገዳሙ የአብነት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ለቆዩ አራት ተማሪዎች የዲቁና ማእረግ በመስጠት አባታዊ መመሪያን አስተላልፈዋል።
በቄለም ወለጋ ሀገረ ስብከት መዋቅራዊ አደረጃጀቱን የጠበቀ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ገለጹ።
በአሁኑ ወቅት ሀገረ ስብከቱ በተረጋጋ መልኩ መዋቅራዊ አንድነቱን በማጠናከር ሥራውን እየሠራ ነው ያሉት ብፁዕነታቸው ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከምዕመናንና ከወጣቶች ጋር ባደረግናቸው ተደጋጋሚ ውይይቶች መዋቅራችንን በማስከበር ሥራዎቻችንን በሚገባ ማከናወን የምንችልበት ስልት ቀይሰን በመሥራት ላይ እንገኛለን፤ ሀገረ ስብከታችንም ፍጹም ሰላማዊና ሥራዎች በመግባባት የሚከናወኑበት ተቋም በመሆን ኃላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።
ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ዙሪያ የተላለፈ የሰላም መልዕክት፧
“ቀብጸት ነፍስየ ሰላመ ወረሳዕክዋ ለሠናይትየ፦ ነፍሴን ከሰላም አራቀ፣ በጎ ነገርን ረሳሁ” (ሰቆ ኤር. 33:17)
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዐሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤትና የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዚዳንት ፲፩ኛ ዓመት መታሰቢያ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በመካሔድ ላይ ይገኛል
የቅዱስነታቸው የሕይወት ታሪክ እንደሚከለው ይነበባል።
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ አምስትና በሕገ ቤተክርስቲያን አንቀጽ 19 ቁጥር 3 አስቸኳይ ጉዳይ ሲያጋጥም ምልዓተ ጉባኤ እንደሚያደርግ በተደነገገው መሠረት ሐምሌ 26ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው አስቸኳይ ምልዓተ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ በተፈጠረው ወቅታዊ የዶግማ፣ የቀኖናና የአስተዳደራዊ ጥሰቶችን አስመልክቶ ውሳኔዎች አሳልፏል፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት አዲስ ለማሰራው ህንፃ ቤተ ክርስቲያን ባርከው የመሠረተ ደንጊያ አኖሩ።
ቅዱስነታቸው ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና ከድሬዳዋ ከንቲባ ከአቶ ከድር ጁሀር ጋር በመሆን በድሬዳዋ ከተማ እንዱስትሪ መንደር አዲስ ለሚሰራው የመካነ ሰማእት ቅዱስ እስጢፋኖስ፣ወልደታ ለማርያምና ወአቡነ ሳሙኤል ህንፃ ቤተ ክርስቲያን የመሠረተ ደንጊያ አኑረዋል፣
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ፤
ሐምሌ ፲፯ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም አዲስ አበባ
በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት የ፲ ዓመት ስልታዊ እቅድ ዙሪያ ለሁለት ቀናት የተካሄደው የምክክር ጉባኤ ተጠናቀቀ::
ከሐምሌ ፲፬-፲፭ ቀን ፳፻፲፭ ዓ ም ለሁለት ቀናት በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት የጉባኤ አዳራሽ በሀገረ ስብከትቦቱ የ፲ ዓመት ስልታዊ እቅድ ዙሪያ የተካሄደው የምክክር ጉባኤ መጠናቀቀ።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም ወቅታዊ የቤተክርስቲያንን ሁኔታ አስመልክቶ የሰላም ጥሪ አተስላለፉ።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወቅታዊ የቤተክርስቲያናችንን ሁኔታ አስመልክቶ ዛሬ ሐምሌ ፲፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም ከቀትር በኋላ በጽ/ቤታቸው ልዩ መግለጫ ተሰጥተዋል።
አዲስ ለሚሾሙት ኤጲስ ቆጶሳት የጸሎተ አስኬማ ሥነሥርዓት ተከናወነ።
በዛሬው ዕለት በተፈጸመው ጸሎተ አስኬማ ለሥርዓቱ የተሠራው ጸሎት በቅዱስነታቸው መሪነት ከደረሰ በኋላ ቡራኬ የተሰጠበትን ቅናተ ዮሐንስ ቅዱስነታቸው ለተሿሚ ቆሞሳት አስታጥቀዋል።