ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
ቅዱስ ሲኖዶስ የትግራይ ሕዝብ ይቅርታ ጠየቀ
ቅዱስ ፓትርያርኩ አልሾምም ወደ ትግራይም ፤ አልሔድም አላሉም
በአንዳንድ ማኅበራዊ ሜዲያዎች ቅዱስ ፓትርያርኩ በቅዱስ ሲኖዶስ “የተመረጡትን መነኮሳት አልሾምም፤ ወደ ትግራይም አልሔድም”ብለዋል ተብሎ የተሰርጭው ዜና ፍጹም ሐሰት ነው። የተመረጡትን አባቶችንም አልሾምም አላሉም። በተያዘው መርሐ ግብር መሠረትም ወደ ትግራይ ይጓዛሉ።
አዲስ በሚሾሙት ኤጲስቆጶሳት የአመራረጥ አካሄድ ዙሪያ በአስመራጭ ኮሚቴ አባላት ብፁዓን አባቶች ማብራሪያ ተሰጠ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የግንቦት ርክበ ካህናት ምልአተ ጉባዔ ለ፯ የኦሮሚያ እና ለ፪ የደቡብ ክልል አህጉረ ስብከት በኤጲስቆጶስነት የሚሾሙ ቆሞሳትን መልምለው ለምልአተ ጉባዔ እንዲያቀርቡ የተመረጡት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ባከናወኑት የምልመላ ሂደት ዙሪያ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ተሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ሲያካሂድ የነበረውን አስቸኳይ ስብሰባ በማጠናቀቅ የተሰጠ መግለጫ
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ የልዑካን ቡድን ሐምሌ ፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ወደትግራይ ርዕሰ ከተማ መቐለ ይጓዛል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ባስ ተላለፈው ውሳኔ መሰረት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የሚመራ የልዑካን ቡድን ሐምሌ ፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ .ም ወደ ክልል ትግራይ ርዕሰ ከተማ መቐለ ይጓዛል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መሪ እቅድ ትግበራ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ።
በግንቦት ፳፻፲፭ ዓ/ም ርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የጸደቀውንና ለቤተክርስቲያናችን መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት መሳለጥ ተጨባጭ ለውጥ ያመጣል ተብሎ የታመነበትን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መሪ እቅድ በሠፊው የሚተነትንና የሚያስረዳ የአንድ ቀን ሥልጠና የመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት አስፈፃሚ አካላት ለሆኑት ለጠቅላይ ጽ/ቤቱ የመምሪያና ድርጅት ኃላፊዎችና ለምክትል ኃላፊዎች ተሰጠ።
የሰኔ ማርያም በዓለ ንግሥ ቅዱስ ፓትርያርክ በተገኙበት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በታላቅ ድምቀት ተከበረ።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት እና ብፁዕ አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ዛሬ ሰኔ ፳፩ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የሰኔ ማርያም በዓለ ንግሥ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በድምቀት ተከበረ ።
የምሥራቅ አውስትራሊያና ኒውዚላንድ ሀገረ ስብከት በጦርነት ጉዳት ለደረሰባቸው አብያተክርስቲያናት ርዳታ ሰጠ።
በኢ.ኦ.ተ.ቤ. የምሥራቅ አውስትራሊያ እና ኒውዚላንድ ሀገረ ስብከት በጦርነትና በተለያዩ ምክንያቶች ጉዳት ለደረሰባቸው አብያተ ክርስቲያናት ማቋቋሚያ የሚሆን የ 2,091,000.00(ሁለት ሚሊየን ዘጠና አንድ ሺ) እርዳታ አበረከተ።
በሰሜን አሜሪካን የሚገኘው ዳግማዊ ደብረ ሊባኖስ ቅዱስ ያሬድና አቡነ ፊሊጶስ ገዳምና የአብነት ትምህርት ቤት ከስልሳ በላይ ታዳጊ ወጣቶችን በመንፈሳዊ የትምህርት ዘርፍ እያሰለጠነ ነው።
በሰሜን አሜሪካን ቨርጂኒያ ግዛት ኪንግ ጆርጅ ካውንቲ የሚገኘው ዳግማዊ ደብረ ሊባኖስ ቅዱስ ያሬድና አቡነ ፊሊጶስ ገዳም አንድ መቶ ሃያ ተማሪዎችን በሁለት ዙር በመቀበል በልዩልዩ መንፈሳዊ ትምህርት ዘርፎች ማስተማር ጀመረ።
የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ/ም የስብከተ ወንጌል እና የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ የጋራ የአገልግሎት ሥምሪት ሥልጠና ተከናወነ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያና የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ በጋራ የሚያስተባብሩት በስብከተ ወንጌል ማስፋፋትና በሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አደረጃጀት ዙሪያ በ፵፰ አህጉረ ስብከት ሥልጠና ለመሥጠት ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለጸ።