ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በህንድ ማላንካራ ሲሪያን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የተከበረውን የቅዱስ ቶማስ 1950ኛ የሰማዕትነት መታሰቢያ በዓል በማስመልከት ቃለ በረከት አስተላለፉ፡፡
ቅዱስነታቸው በዛሬው ዕለት በህንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በከፍተኛ ድምቀት የተከበረውን የሐዋርያው የቅዱስ ቶማስ የሰማዕትነት መታሰቢያ በዓል በማስመለከት በበዓሉ ላይ እንዲገኙ ከብፁዕ ወቅዱስ ባስልዮስ ማር ቶማ ማቴዎስ ሦስተኛ የህንድ ማላንካራ ሲሪያን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የክብር ጥሪ ተደርጎላቸው የነበረ ቢሆንም ቅዱስነታቸው በአካል ለመገኘት አስቀድሞ በተያዘ መርሐ ግብር ምክንያት ስላልቻሉ በቋሚ ሲኖዶስ በተወከሉ ልዑካን አማካኝነት አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የካቲት 18 ቀን 2016 ዓ/ም የሚጀመረውን ጾመ ነነዌ በማስመልከት አባታዊ ቃለ በረከት አስተላለፉ፡፡
በመረሻም ታላቅ ሀገር ይዘን፣ ምድሩ ሳይጠበን አመል እያጋፋን ነውና ጾማችን፣ጸሎታችን ቅድመ እግዚአብሔር ደርሶ ለሀገር ደኅንነት፣ ለሕዝብ ድኅነት እንዲያመጣልን እግዚአብሔር ይቅር ብሎን ዘመኑን በምሕረት ያሻግረን ዘንድ በታላቅ ንስሐ፣ በጸሎትና በአስተብቍዖት ወደ እግዚአብሔር እንድንቀርብ አባታዊ መልእክታችንን በመሐሪው አምላክ ስም እናስተላልፋለን።
በግፍ የተገደሉት የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም አባቶች አስክሬን ተረሽነው ከተቀበሩበት ከጊዳ ተክለሃይማኖት አካባቢ ተነስቶ በገዳሙ በክብር ሥርዓተ ቀብር ተፈጸመ።
የካቲት ፲፮ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
በታላቁ ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የተፈፀመውን ጥቃት አስመልክቶ በምሥራቅ ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተመራ ውይይት ተካሄደ፡፡
የካቲት ፲፭ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
በ81 ዓመታቸው በድንገተኛ የመኪና አደጋ ያረፉት የሊቁ የመምህር ገብረ ዮሐንስ ገብረ ማርያም ሥርዓተ ቀብር ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በሚገኘው የበዓለወልድ ቤተክርስቲያን ተፈጸመ።
የካቲት ፲፪ ቀን ፲ወ፮ ዓ.ም
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ የዮርዳኖስ መንግሥት የቱሪዝም እና ጥንታዊ ቅርሶች ሚኒስትር ክቡር ማክራም ሙስጣፋ አብዱልከሪምን በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተቀብለው አነጋግረዋል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የካቲት ፲፫/፳፻፲፮ ዓ/ም የዮርዳኖስ መንግሥት የቱሪዝምና የጥንታውያት ቅርሶች ሚንስትር ክቡር ማክራም ሙስጠፋ አብዱልከሪምን በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተቀብለው አነጋግረዋል።
ሰሞኑን በማኅበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወረ ስለሚገኘው “መነኩሴ “ነኝ ባይ ግለስብ በሀገረ ስብከቱ የማይታወቅ መሆኑን ሀገረ ስብከቱ ገለጸ።
የአርሲ ሀገረ ስብከት ሰሞኑን በማኅበራዊ ድረ ገጾች ራሱን “መነኩሴ”በማስመሰልና በአርሲ ሀገረ ስብከት አገልጋይ እንደሆነ በመግለጽ የሚንቀሳቀሰውን ግለሰብ የማያውቀውና ሐሰተኛ “መነኩሴ” መሆኑን ለጠቅላይ ቤተክህነት በጻፈው ደብዳቤ አስታወቀ።
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተላለፈ ወቅታዊ መልዕክት።
ዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም:- የካቲት 12 ቀን በታጣቂ ቡድኖች ከተወሰዱ በኋላ አራቱም በትላንትናው አለት የተገደሉ ሲሆን አባ ኪዳነማርያም ገ/ሰንበት የተባሉት አባት ቆስለው በገዳሙ እንደሚገኙ ታውቋል።
በኦስሎ ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምርህታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ደቀመዛሙርት ማዕርገ ዲቁና ተቀበሉ።
በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ኤልያስ መልካም ፈቃድ አሳሳቢነት የአብነት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ለቆዩት አራት ደቀ መዛሙርት የዲቁና ሥልጣነ ክህነት በሰጡበት ወቅት ለአገልጋዮቹ በሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ትምህርት አስተምረው በዓለም ዙሪያ ያለችውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን በቅንነትና በእውቀት እንዲያገለግሏትም አባታዊ መመሪያም አስተላልፈዋል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ የካቲት 11/06/2016 ዓ/ም ለሰባት ማኅበራት የዕውቅና ሰርተ ፍኬት ሰጠ።
የተሰጣቸው ሰርተፍኬት ለሦስት ተከታታይ ዓመታት ይቆያል ተብሏል።