ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች

የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በዓለ ዕረፍቱ በወናጎ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን በታላቅ መንፈሳዊ ክብርና ድምቀት ተከበረ !!!

መስከረም 2/2017 ዓ.ም

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ዛሬ መስከረም 2 ቀን 2017 ዓ.ም. ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር አካሄደ።

መስከረም 2 ቀን 2017 ዓ.ም.

በከሚሴ ሀገረ ስብከት የከሚሴ ቅዱስ ገብርኤልና ቅዱስ ሚካኤል ሰበካ ጉባኤ የ2017 ዓ.ም አዲስ ዓመትን እና የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስን መታሰቢያ በዓል በታላቅ ድምቀት ተከበረ።

ወትባርክ አክሊለ ዓመተ ምህረትከ ወይጸግቡ ጠላተ ገዳም(በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል) መዝ 65:-11

ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ አብርሃም አዲስ ዓመትን አስመልክተው የእንኳን አደረሳቸው መልእክት አስተላለፉ።

በዓሉን ስናከብር የተራበውን በመመገብ የተጠማውን በማጠጣት፣ የተቸገረውን በመርዳት፣ ታመው በየሆስፒታሉ ያሉትን እግዚአብሔር ይማራችሁ ብሎ በመጎብኘት፣ እንዲሁም በየማረሚያ ቤቱ እግዚአብሔር ያስፈታችሁ በማለት በዓሉን እንድናከብረው የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጥሪ ነው።

የመጥምቀ ክርስቶስ ቅዱስ ዮሐንስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በድምቀት ተከብሯል (ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት)

ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ በበዓሉ ለተገኙ ምእመናን ዕለቱን አስመልክተው ትምህርትና ቃለ ምእዳን አስተላልፈዋል።

በዲላ ጎላ ቅዱስ ራጉኤል ቤተክርስቲያን ዓመታዊ የቅዱስ ሩጉኤል ክብረ በዓል በታላቅ መንፈሳዊ ክብርና ድምቀት  ተከበረ።

መስከረም 1/2017 ዓ.ም

በሲዳማ ሀገረ ስብከት በሀዋሳ ከተማ በሰአሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የታላቁ መልአክ የቅዱስ ራጉኤል በዓል በታላቅ ድምቀት ተከበረ።

መስከረም 1/2017 ዓ/ም

በኢ/ኦ/ተ/ቤ በሰሜን አሚሪካ የኮሎራዶ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ቡራኬ

ጳጉሜን ፭ ፳፻፲፯ ዓ/ም

ምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በእስር ላይ ለሚገኙ የሕግ ታራሚዎች ለአዲሱ ዓመት ፳፻፲፯ ዓ.ም መዋያ የሚሆን የበሬ ሥጦታ አበረከተ።

ጳጉሜን ፭ ፳፻፲፯ ዓ/ም

“ካለፈው ዓመት ስህተት ወደ አዲሱ ዓመት እንዳይሸጋገር ማድረግ እና ለሁለንተናዊ ለውጥ ራስን ማዘጋጀት ይኖርብናል”። ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ

የዘመናት ባለቤት እግዚአ ሰማያት ወምድር ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለ 2017 ዘመነ ማቴዎስ የምሕረት ዓመት በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ

በፌስቡክ ያግኙን

የኅትመትና ሚዲያ ዋና ክፍል

ብፁዕ አቡነ አብርሃም

የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ

በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ

ለውስጥ አገልግሎት

የኢሜይል አገልግሎት

ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን

ርእይ

ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት

ተልእኮ

  • የእግዚአብሔርን ቃል ለሰው ልጆች ሁሉ ማስተማርና ማዳረስ

  • ሰውን በሁለንተናዊ ሰብእናው ማገልገልና ማዳን

  • ሰውን ሁሉ በነገረ መለኮትና በነገረ ጥበብ ትምህርት በማልማት በመንፈሳዊም ሆነ በሥጋዊ ሕይወቱ የተሻለ ኑሮ እንዲኖረው ማድረግ

  • ጥራትና ብቃት፣ ፍትሐዊነትና እኩል ተደራሽነት ያለው መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ለሰው ሁሉ ማበርከት

  • የተለያዩ የልማት መርሀ ግብሮችን በመንደፍ ቤተ ክርስቲያንን በኢኮኖሚ ማበልጸግ

  • በቴክኖሎጂ ስልት የሚመራና አዋጭነቱ አስተማማኝ የሆነ የጠቅላላ ሀብት አስተዳደርና አጠቃቀም እንዲረጋገጥ ማድረግ

  • የሰው ልጆች ሁሉ እኩልነት፣ ሰላምና ፍትሕ፣ ፍቅርና ስምምነት እንዲጠበቅ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ

  • የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አሰራር ግልጽ፣ ለሁሉም ተደራሽና ችግር ፈቺ እንዲሆን ማድረግ

ዕሴቶች

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅሊናን የሚረታ፣ አእምሮን የሚመሥጥ፣ ከጥንተ ፍጥረት ተነሥቶ በዘመነ አበው በሕገ ልቡና፣ በዘመነ ብሉይ በሕግ ኦሪት፣ ተራምዶ መዳረሻውን ሕገ ወንጌል ያደረገ ጥንታዊ ክርስቶሳዊና ሐዋርያዊ ትምህርተ ሃይማኖት፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን፣ በያሬዳዊ ጣዕመ ዜማ የታጀበ ሥርዐተ አምልኮ፣ በጽሑፍና በትውልድ ቅብብሎሽ የተወረሰ የረጅም ጊዜ ትውፊት ባህልና ታሪክ

  • በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የበለጸገ፣ እግዚአብሔርን የሚወድና የሚፈራ ለእግዚአብሔር የሚታዘዝና ምክረ ካህን የሚቀበል ከስልሳ ሚልዮን በላይ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ

  • ለምጣኔ ሃብት ዕድገት እጅግ የምትጠቅም በውብ ሥነ ተፈጥሮና በሥነ ጽሑፍ፣ በሥነ ጥበብና በኪነ ጥበብ፣ በታሪክና በቅርስ ሃብት የበለጸገች እንዲሁም በሃይማኖት፣ በነጻነትና በአንድነት የደመቀች ሃገር

  • የእግዚአብሔርን ቃል ከሃገር ውስጥ ባሻገር ለመላው ዓለም ማዳረስ የሚችሉ ከግማሽ ሚልዮን ያላነሱ ሊቃውንት፣ ቀሳውስት፣ ዲያቆናት፣ ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ከሁለት ሺሕ ያላነሱ ገዳማት

  • መላውን ዓለም እያዳረሰና እየሰፋ የሚገኝ ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ የተዋቀረ ጠንካራ መዋቅር ያላት መሆኗ

ያግኙን

+251 111 55 0098 P.O.Box 1283 A.A. 5 KILLO, ADDIS ABABA, ETHIOPIA በፌስቡክ ያግኙን የዩትዩብ ቻነል