ልማት በቤተ ክርስቲያን

ልዮ ዕትም መጽሔት

ይህ ”ልማት በቤተክርስቲያን“ የተሰኘ ልዮ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።

ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች

በሲዳማ ሀገረ ስብከት የ2017 ዓ/ም የመስቀል በዓል ዝግጅትን አስመልክቶ በብፁዕ አቡነ ዮሴፍ ሰብሳቢነት ውይይት ተደረገ።

መስከረም 14/2017 ዓ/ም

የጉባላፍቶ ወረዳ ቤተክህነት የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤውን አካሒዷል

በ2016 የአገልግሎት ዓመት ወረዳ ቤተክህነቱን ጨምሮ በገዳማት፣ አድባራትና አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት የተከናወኑ የተግባራት አፈጻጸም ሪፖርትና የሀገረ ስብከቱን ዓመታዊ እቅድ መነሻ በማድረግ የተዘጋጀውን የወረዳ ቤተክህነት የ2017 ዓ.ም ዓመታዊ እቅድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የመስቀል ደመራ በዓል ፍጹም ደማቅ እና ሰላማዊ ሆኖ እንዲከበር የከተማ አስተዳደሩ እያደረገ ላለው ስራ ምስጋና አቅርበዋል።

መስከረም ፲፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም
“””””””””””””””””””””””””””””””””””””””””””””
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ

በኮቸሬ ገደብና ጮርሶ ወረዳ ቤተክህነት የሰንበት ት/ቤት አንድነት ተመሠረተ!!!

የሀገረ ስብከቱ የስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ ሊቀትጉሃን ቀሲስ ሀብታሙ አበበ  ከፊት ይልቅ ትጉ!! በ፪ኛ ጴጥ ፪:፲ ያለውን አምላካዊ ቃል መነሻ በማድረግ የሰንበት ት/ቤት አባላት መጠራታቸውን መመረጣቸውን በመመልከት ከበፊት ይልቅ መትጋትና የቅድስት ቤተክርስቲያን ሥርዓት በመጠበቅና በማስጠበቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ በሰፊው አስተምረዋል።

የቤተክርስቲያን ተወካዮች በግብፁ ጉባኤ ላይ ያልተገኙት በግል በገጠማቸው እክል ምክንያት መሆኑን የውጭ ግንኙነቱ መምሪያ አስታወቀ።

መስከረም ፲ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም

በሲዳማ ሀገረ ስብከት ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በጠቅላይ ቤተ ክህነት የወጣውን የማኅበራት አስተዳደር ደንብ አስመለክቶ የምዝገባ ጥያቄ ላቀረቡ አሥራ ሁለት ማኅበራት ስልጠና ተሰጠ።

መስከረም 9/2017 ዓ/ም

በምሥራቅ ሐረርጌ ሀ/ስብከት በመንበረ ጵጵስና ጌቴሴማኔ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም መንበረ ጵጵስና አዳራሽ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ልዑካን የደብል ኢንትሪ የሒሳብ አያያዝ የግማሽ ቀን ሥልጠና እየተከናወነ ይገኛል።

መስከረም ፱ ፳፻፲፯ ዓ.ም
ምሥራቅ ሐረርጌ ፣ ኢትዮጵያ

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅሊይ ቤተክነት አስተዳደር ጉባኤ በአዱስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን የሚያጠኑ ፯ አባላት ያሉት ኮሚቴ ሰየመ፡፡

መስከረም ፱ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም

በአዲሱ ዓመት ቅድስት ቤተክርስቲያን ትኩረት ሰጥታ መሥራት ያለባትን ጉዳዮች ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል ሊቀጳጳስ አስታወቁ።

መስከረም 06 ቀን 2017 ዓ/ም
አሶሳ፤

በፌስቡክ ያግኙን

የኅትመትና ሚዲያ ዋና ክፍል

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ

የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ

የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ልማት በቤተ ክርስቲያን

ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።

ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን

ርእይ

ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት

ተልእኮ

  • የእግዚአብሔርን ቃል ለሰው ልጆች ሁሉ ማስተማርና ማዳረስ

  • ሰውን በሁለንተናዊ ሰብእናው ማገልገልና ማዳን

  • ሰውን ሁሉ በነገረ መለኮትና በነገረ ጥበብ ትምህርት በማልማት በመንፈሳዊም ሆነ በሥጋዊ ሕይወቱ የተሻለ ኑሮ እንዲኖረው ማድረግ

  • ጥራትና ብቃት፣ ፍትሐዊነትና እኩል ተደራሽነት ያለው መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ለሰው ሁሉ ማበርከት

  • የተለያዩ የልማት መርሀ ግብሮችን በመንደፍ ቤተ ክርስቲያንን በኢኮኖሚ ማበልጸግ

  • በቴክኖሎጂ ስልት የሚመራና አዋጭነቱ አስተማማኝ የሆነ የጠቅላላ ሀብት አስተዳደርና አጠቃቀም እንዲረጋገጥ ማድረግ

  • የሰው ልጆች ሁሉ እኩልነት፣ ሰላምና ፍትሕ፣ ፍቅርና ስምምነት እንዲጠበቅ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ

  • የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አሰራር ግልጽ፣ ለሁሉም ተደራሽና ችግር ፈቺ እንዲሆን ማድረግ

ዕሴቶች

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅሊናን የሚረታ፣ አእምሮን የሚመሥጥ፣ ከጥንተ ፍጥረት ተነሥቶ በዘመነ አበው በሕገ ልቡና፣ በዘመነ ብሉይ በሕግ ኦሪት፣ ተራምዶ መዳረሻውን ሕገ ወንጌል ያደረገ ጥንታዊ ክርስቶሳዊና ሐዋርያዊ ትምህርተ ሃይማኖት፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን፣ በያሬዳዊ ጣዕመ ዜማ የታጀበ ሥርዐተ አምልኮ፣ በጽሑፍና በትውልድ ቅብብሎሽ የተወረሰ የረጅም ጊዜ ትውፊት ባህልና ታሪክ

  • በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የበለጸገ፣ እግዚአብሔርን የሚወድና የሚፈራ ለእግዚአብሔር የሚታዘዝና ምክረ ካህን የሚቀበል ከስልሳ ሚልዮን በላይ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ

  • ለምጣኔ ሃብት ዕድገት እጅግ የምትጠቅም በውብ ሥነ ተፈጥሮና በሥነ ጽሑፍ፣ በሥነ ጥበብና በኪነ ጥበብ፣ በታሪክና በቅርስ ሃብት የበለጸገች እንዲሁም በሃይማኖት፣ በነጻነትና በአንድነት የደመቀች ሃገር

  • የእግዚአብሔርን ቃል ከሃገር ውስጥ ባሻገር ለመላው ዓለም ማዳረስ የሚችሉ ከግማሽ ሚልዮን ያላነሱ ሊቃውንት፣ ቀሳውስት፣ ዲያቆናት፣ ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ከሁለት ሺሕ ያላነሱ ገዳማት

  • መላውን ዓለም እያዳረሰና እየሰፋ የሚገኝ ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ የተዋቀረ ጠንካራ መዋቅር ያላት መሆኗ

ያግኙን

+251 111 55 0098 P.O.Box 1283 A.A. 5 KILLO, ADDIS ABABA, ETHIOPIA በፌስቡክ ያግኙን የዩትዩብ ቻነል የቴሌግራም ቻነል