ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ አገር እንዳይገቡ ተከለከሉ።
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአሜሪካ የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎት ጨርሰው ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ እንዳይገቡ መከልከላቸው ተሰምቷል።
የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት እና የውጭ ግንኙነት መምሪያ ሓላፊዎች ከእስራኤል አምባሳደር ጋር ተወያዩ።
የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጸሐፊ ክቡር መልአከ ሕይወት ቆሞስ አባ ኃይለገብርኤል ነጋሽ እና የውጭ ግንኙነት መምሪያ ሓላፊ ሊቀ ካህናት ደረጀ መንግሥቱ በኢትዮጵያ ከእስራኤል አምባሳደር ክቡር አለልኝ አድማሱ እና የኤምባሲው ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ተወያይተዋል ።
ማኅበረ ቅዱሳን በዳውሮ ሀገረ ስብከት አዳሪ የአብነት ት/ቤት አስመረቀ።
በማኅበረ ቅዱሳን አስተባባሪነት በዳውሮ ሀ/ስብከት በምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም የተገነባው አዳሪ የአብነት ት/ቤት ጥር 23 ቀን 2016 ዓ.ም የዳውሮና ኮንታ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ፣ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የአካባቢው ምእመናን በተገኙበት ተመርቋል።
የመርካቶ ደብረ አሚን ዳግሚት ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ሕንጻ ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ቤት ተከበረ።
በትናንትናው ዕለት የእድሳት ሥራው ተጠናቆ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ተባርኮ መንፈሳዊ አገልግሎት መስጠት የጀመረው ታለቁ ገዳም በዛሬው ዕለት ብፁዕ አቡነ ቶማስ የአዊ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ታቦተ አቡነ ተክለሃይማኖት ዑደት በማድረግ በዓሉን ለማክበር የተሰበሰቡ ውሉደ ክህነትና ውሉደ ጥምቀትን በመባረክ በዓሉ ተከብሯል።
የመርካቶ ደብረ አሚን ዳግሚት ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ሕንጻ ቤተክርስቲያን እድሳት ተጠናቆ በብፁዕ ወቅዱስ አባታችን ተባርኮለአገልግሎት መስጠት ጀመረ።
በ፲፰፻፺ወ፰ ዓ/ም በንጉሠ ነገሥት አጼ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት የተመሠረተውና ፻፲፰ ዓመታት ያስቆጠረው ሕንጻ ቤተመቅደስ በእድሜ ርዝመት ምክንያት በመጎዳቱ ምክንያት ለመንፈሳዊ አገልግሎት አመቺ በሆነ መንገድ እድሳት ተደርጎለት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ተባርኮ መንፈሳዊ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።
አገር አቀፍ የስብከተ ወንጌል አልግሎትን ለማጠናከር የሚያስችል የምክክር መድረክ ተካሔደ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ አገር አቀፍ የስብከተ ወንጌልን አገልግሎት በተጠና፣ተቋማዊ በሆነና ለውጥ ሊያመጣ በሚያስችል መልኩ ማከናወን የሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከሚመለከታቸው አካላትና ከስባቱ ክፍላተ ከተማ ሥራ አስኪያጆችና የስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊዎች ጋር ጥር ፲፮ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መሰብሰቢያ አዳራሽ የምክክር መድረክ አካሔደ።
በቦሰት ወረዳ ቤተ ክህነት የመርቆ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ፡መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን ባልታወቁ የታጠቁ ኃይሎች ተቃጥሏል፡፡
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በቦሰት ወረዳ ቤተ ክህነት የመርቆ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን በአሳዛኝ ሁኔታ ባልታወቁ የታጠቁ ኃይሎች ትናንት ጥር 17/2016 ዓ.ም አመሻሽ ላይ ተቃጥሏል፡፡
“ችግር እና መከራ ሁሉ ጊዜያዊ ነው፤ በእምነት በመጽናት ችግርን የምናልፍ አስተዋዮች መኾን አለብን”ብፁዕ አቡነ አብርሃም
በየዓመቱ በባሕር ዳር ከተማ በድምቀት የሚከበረው” የቅዱስ ጊዮርጊስ ስባር አጽሙ” ሃይማኖታዊ በዓል ዛሬም በድምቀት እየተከበረ ነው።
የዴንቨር ኮሎራዶና አካባቢው ሀገረ ስብከት ፮ኛው የሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ በመካሔድ ላይ ነው።
በሰሜን አሜሪካ በዴንቨር ከተማ በዛሬው ዕለት የሀገረ ስብከቱ ፮ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ መካሔድ ጀመረ። በ፮ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ የተገኙት የዴንቨር ኮሎራዶና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ጉባኤውን በፀሎት የከፈቱት ሲሆን ጉባኤውንም በርዕሰ መንበርነት እየመሩት ይገኛሉ።
በጋምቤላ ሀገረ ስብከት በጋምቤላ ከተማ ባሕረ ጥምቀት ለአምስት ቀናት ሲካሄድ የሰነበተው የስብከተ ወንጌል ጉባኤ ተጠናቀቀ።
ከበዓለ ጥምቀት ማለትም ከጥር 10 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ሲከናወን የሰነበተው የስብከተ ወንጌልና የመዝሙር አገልግሎት በደመቀ ዝግጅት ተጠናቋል።