የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በአሮጌው ቄራና በጠቅላይ ቤተክህነት በግንባታ ላይ የሚገኙትን ሕንጻዎች የሥራ አፈጻጸም ተዘዋውረው ተመለከቱ።

March 24, 2024

መጋቢት ፲፭ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
+++++++++++++++++++
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
==============

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃመረ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአሮጌው ቄራና በጠቅላይ ቤተክህነት በመገንባት ላይ ያሉትን ሕንጻዎች የሥራ አፈጻጸም  ተዛውረው ከተመለከቱ በኋላ በቀጣይ ሥራዎች ዙሪያ መመሪያ ሰጥተዋል።

ብፁዕነታቸው በአሮጌው ቄራ በመገንባት ላይ የሚገኙትን  ሁለት ሕንጻዎች ተዘዋውረው ከተመለከቱ በኋላ የግንባታ ሥራዎቹ  በፍጥነት ተጠናቀው አገልግሎት ላይ መዋል ይችሉ ዘንድ የሕንጻ ሥራ ተቋቋራጮቹ ፣ተቆጣጣሪዎቹና የግንባታ ሥራውን በቅርበት የሚከታተለው የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት የሥራ አመራሮች የግንባታ ሥራው ጥራትና ፍጥነትን መሰረት በማድረግ የሚከናወንበትና  ሥራው በፍጥነት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት የሚችልበትን ስልት ተከትለው እንዲሰሩ አደራ ብለዋል።
በግንባታ ሥራዎቹ የሚስተዋሉ ችግሮች ሁሉ መወገድ እንዲችሉም ተናቦና ተግባብቶ መስራት እንደሚገባ የገለጹት ብፁዕነታቸው በግንባታ ሥራው ሂደት የሚስተዋሉ ችግሮችን በመንቀስ እንዲታረሙና  ለግንባታ ሥራ ተቋራው ፍጥነትና ጥራትን መሰረት በማዶረግ እንዲሰራ አመራር ሰጥተዋል።

በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት በመገንባት ላይ የሚገኘው ዘመናዊ፣ግዙፍና ሁለገብ አዳራሽ የሥራ ሂደትን የተመለከቱት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የግንባታ ሥራው በመልካም አፈጻጸም ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።ብፁዕነታቸው ሠላሳ አራት ፐርስንት ላይ ደርሶ የተረከቡት ይኸው የግንባታ ሥራ የፕላን ማሻሻያ የተደረገበት ሲሆን ይኸንኑ ተከትሎ በተገኘው  ከሦስት መቶ ካሬ ሜትር  በላይ በሆነው ትርፍ ቦታ ላይ ዘመናዊና ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን ያሟላ የቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ በሁለገብ አዳራሹ ውስጥ ተካቶ እንዲሰራ መደረጉን ገልጸዋል።

በግንባታ ላይ የሚገኘው ሁለገብ ዘመናዊ አዳራሹ ዋናውን አዳራሽ ጨምሮ የቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ፣መጠነኛ አዳራሾች፣ቢሮዎች፣የመኪና ማቆሚያ ቦታዎችን ያሟላና ዓለም አቀፋዊ ጉባኤዎችን ለማካሔድ ምቹ የሆነ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም የማጠቃለያ ሥራዎች ላይ የሚገኝ ከቤተክርስቲያናችን ግዙፍ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ እንደሆነም ይታወቃል።በአሮጌው ቄራ በመገንባት ላይ የሚገኙት ሕንጻዎችም በሚጠናቀቁበት ወቅት በከተማችን የሚስተዋለውን የመኖሪያ ቤት እጥረት በመቀነስ ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የአመራር ብቃትን ለማሳደግና ዘመኑን የዋጀ የአሰራር ሥርዓትን ለመዘርጋት የሚያስችል የምክክር ጉባኤ በጠቅላይ ቤተክህነት በመካሔድ ላይ ነው። Link to: የአመራር ብቃትን ለማሳደግና ዘመኑን የዋጀ የአሰራር ሥርዓትን ለመዘርጋት የሚያስችል የምክክር ጉባኤ በጠቅላይ ቤተክህነት በመካሔድ ላይ ነው። የአመራር ብቃትን ለማሳደግና ዘመኑን የዋጀ የአሰራር... Link to: የመልአከ ፀሐይ መኰንን ደስታ ግብአተ መሬት ተፈጸመ። Link to: የመልአከ ፀሐይ መኰንን ደስታ ግብአተ መሬት ተፈጸመ። የመልአከ ፀሐይ መኰንን ደስታ ግብአተ መሬት ተ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top