ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ለ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የትንሳኤ በዓል ያስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ሙሉ ቃል እነሆ፤
የገብረ ሰላመ በዐል በታላቅ ድምቀት ተከበረ።
የ፳፻ ፲ወ ፭ ዓ.ም የገብረ ሰላመ በዐል በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፣ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ፣ክቡር ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት መ/ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የጠቅላይ ቤተክህነት የየመምሪያውና የየድርጅቶቹ ኃላፊዎች፣ክቡር ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ ጸጋዬ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ አምባሳደር ሬሚ Remi Marechaux በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር፣የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ምዕመናንና ምዕመናት በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ሥነሥርዓት ተከብሯል።
የሆሳዕና በዓል በተለያዩ አህጉረ ስብከት በታላቅ ሃይማኖታዊ ሥርዓት በድምቀት ተከበረ።
የሆሣዕና በዓል በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሯል።
በምስራቅ አፍሪካ ሀገረ ስብከት በሱዳን መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የተከሰተውን አለመግባባት አጥንተው የውሳኔ ሀሳብ የሚያቀርቡ የሥራ ኃላፊዎች ካርቱም ገቡ።
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ በሱዳን ካርቱም የሚገኘው መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አስተዳደርና በህዝበ ክርስቲያኑ መካከል የተከሰተውን አለመግባባት በማስመልከት በዝርዝር አጣርተው የውሳኔ ሀሳብ እንዲያቀርቡ የተመደቡት ሦስቱ የቤተክርስቲያናችን የሥራ ኃላፊዎችና የአስተዳደር ጉባኤ አባላትም ሥራቸውን ለማከናወን ካርቱም ገብተዋል።
ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በባሻ ወልዴ ችሎት የግንባታ ሥራው የተጠናቀቀውን ሕንጻ ቁልፍ ተረከቡ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የኢኮኖሚ አቅሟን በተለያዩ የልማት ሥራዎች በማጎልበት ተቀዳሚ ተልዕኮዋ የሆነውን ስብከተወንጌልን ማስፋፋት፣የገጠር አብያተክርስቲያናትን የማጠናከር፣የአብነት ትምህርት ቤቶችን የማስፋፋትና የማጠናከር ሥራዋን ለማቀላጠፍ ያስችላት ዘንድ በተለምዶ ባሻ ወልዴ ችሎት በመባል በሚታወቀው ቦታ ላይ በአንድ ዓመት ውስጥ ያስገነባችው ዘመናዊ አፓርታማ ተጠናቆ በዛሬው ዕለት የቁልፍ ርክክብ ተደርጓል።
ብፁዕ አቡነ ድሜጥሮስ የአቡዳቢ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራልን የአገልግሎት ፈቃድ ሰነድ ተረከቡ።
ብፁዕ አቡነ ዲሜጥሮስም የኢሜሬትስ መንግሥት ላደረጉት በጎነት ምስጋና ካቀረቡ በኋላ ኢሜሬትስ የነጻነት ምድር፣ የሰላም ሀገር፣ የእስልምና አማናዊ መልክ፣ የስደተኞች ማረፊያ፣ እድገት ከባህል፣ ሥልጣኔ ከሞራል ጋር የተባበሩባት ናት ብለዋል። ወደ ፊት በሚኖረው ፍላጎትም ዙሪያ እገዛቸውን ጠይቀዋል።
በመንበረ ፓትርያክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የተዋቀረው የትምህርትና ስልጠና ግብረ ኃይል ዐቢይ ኮሚቴ የሰባክያነ ወንጌል ስምሪት አከናወነ፡
መጋቢት ፳፪ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ በተከናወነው መርሐ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተገኝተው በስምሪቱ ለሚሳተፉ አካላት መመሪያ አስተላልፈዋል፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
ጥር 14 ቀን 2015ዓ.ም. በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሐሮ ባለወልድ ቤተ ክርስቲያን የተፈጸመውን ሕገወጥ የኤጲስ ቆጶሳት ሹመትን ተከትሎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጥር 18 ቀን 2015ዓ.ም. ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የተከናወነው ድርጊት የቤተ ክርስቲያኒቱን ዶግማ፣ ቀኖና አስተዳደራዊ መዋቅር የጣሰ ሕገወጥ አድራጎት መሆኑን አጽንኦት ሰጥቶ በመወያየት ሕገወጡን ሹመት ያከናወኑትና ተሿሚዎችን በቤተ ክርስቲያናችን ቀኖናዊ ሥርዓት ከዲቁና ጀምሮ የነበራቸውን ማዕረገ ክህነት በሙሉ በመሻር ከቤተ ክርስቲያኒቱ አባልነት አውግዞ መለየቱ የሚታወስ ነው፡፡
ላለፉት ፯ ዓመታት ግንባታቸው የተጓተቱ ሁለት ህንጻዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ የሚያደርግ የውል ስምምነት ተፈረመ።
በመርሐ ግብሩ ላይ ሥራውን ቀግንባር ቀደምነት የሚያስተባብሩና የሚመሩት የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ መዊዕ ቀሲስ ሳሙኤል እሸቱና የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የበጀትና ሒሳብ መምሪያ ዋና ኃላፊ ወ/ሮ ጽጌሬዳ ዓለሙ ተገኝተዋል።
“እኛ ካህናት አስታራቂዎች እንጂ ታራቂዎች መሆን አልነበረብንም፤ በጥሪአችን መሰረት የእውነት ካህናት በመሆን ለቤተክርስቲያን አንድነት መስራት ይኖርብናል፤”
በቅርቡ በቤተክርስቲያን ላይ ተፈጥሮ የነበረውን ችግር ነገ ላይ ሆነን ስናየው መጸጸታችን አይቀርም፤የዛሬ አመጣጣችሁ የመጨረሻ እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ።