የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ “ሐዋርያዊ ተልእኳችን ለዘመናችን “በሚል ርእስ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣በሰሜን አሜሪካ የኒዎርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ከጠቅላዮ ቤተ ክህነት ጀምሮ እስከ ክፍላተ ከተማ ለተውጣጡ የወንጌል መምህራን የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጠ።

November 8, 2023

አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
***
ጥቅምት ፳፯ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ዓ.ም
“””””””””””””””””””””””””””””””

በስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ በኩል በ2016 ዓ/ም ሊሠሩ በታቀዱ ቀጣይ የሥራ ተግባራት ረቂቅ ጽሑፍ ላይ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጀምሮ እስከ ክፍላተ ከተማ ከሚገኙ የወንጌል መምህራን ጋር ለአንድ ቀን የቆየ ሥልጠናና ውይይት አካሂዷል።

በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 44ንዑስ ቁጥር 4ላይ ከተዘረዘሩት የአስፈጸሚነትና የአስተዳደር ሥራዎችን ከሚመሩ 18መምሪያዎች አንዱ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ነው።

የቤተ ክርስቲያንም ዋና ተልእኮዋ ስብከተ ወንጌልን በማስፋፋት ምእመናንን ለእግዚአብሔር መንግሥት ማብቃት ነው።

ሌሎቹ መምሪያዎችም ዋና ተልእኳቸው ለስብከተ ወንጌል ድጋፍ መስጠትና ረዳት ሆነው ስብከተ ወንጌልን ማስፋፋት ነው።

በመሆኑም መምሪያው ይህንን ተልእኮ አጠናክሮ ለመቀጠል ካቀዳቸው ቀጣይ የሥራ ተግባራት መካከል የሥምሪት፣የሥልጠና፣የሚድያ እና የሥነ ጽሑፍ ክፍሎችን በማዋቀር ከመንበረ ፓትርያርክ እስከ አጥቢያ ድረስ ባሉት መዋቅሮች ሰባክያነ ወንጌልን በማሠማራት ለምእመናን የስብከተ ወንጌል አገልግሎት መስጠት በመሆኑ ይህንኑ ተግባር አጠናክሮ ለመሥራት ይረዳ ዘንድ ጥቅምት 26 ቀን 2016 ዓ/ም ቦሌ በሚገኘው የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ሕንጻ ከመምሪያው ጀምሮ እስከ ክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ድረስ የሚገኙትን የወንጌል መምህራን በማሰባሰብ ለአንድ ሙሉ ቀን የቆየ ስብከተ ወንጌል ተኮር ሥልጠና የተሰጠ ሲሆን በተጨማሪም በመምሪያው በኩል በ2016 ዓ/ም ሊሠሩ በታቀዱት ቀጣይ የሥራ ተግባራትን አስመልክቶ ሰፋ ያለ ውይይት ተካሂዷል።

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በሰጡት አባታዊ አስተያየት ቤተ ክርስቲያን ስብከተ ወንጌልን የማስፋፋት ተቀዳሚ ሥራዋ ሲሆን ዋና ግቡና ዓላማው ምእመናንን ለእግዚአብሔር መንግሥት ማብቃት ነው ያሉ ሲሆን ይሁን እንጂ ወንጌል ከጥቅም ጋር አብሮ ሊሄድ የማይችል ስለሆነ ሕይወት የሚሰጠውን ወንጌል ከጥቅም ጋራ ከተያያዘ ውጤታማ ለመሆን ያዳግታል ብለዋል።

ብፁዕነታቸው አያይዘው እንደገለጹት አገልጋዮች ደመወዝ እንደሚያስፈልጋቸው ቢታወቅም አገልግሎታቸው ግን ከሚያገኙት ጥቅም በላይ ሊሆን ይገባል ብለዋል።

ብፁዕነታቸው ጨምረው እንደገለጹት የወንጌል መምህራን ጥቅማጥቅምን በመፈለግ ወንጌል ለመስበክ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ልውጥ ለማምጣት አዳጋች ይሆናል ብለዋል።

መልአከ ሰላም ዶክተር አባ ቃለጽድቅ ሙሉጌታ
የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ዋና ሐላፊ በበኩላቸው እንደገለጹት ስብከተ ወንጌልን ለማስፋፋት ጥረት በምናደርግበት ጊዜ ሁሉ በርካታ ፈተናዎች ሊያጋጥሙን ይችላሉ።
ሆኖም ፈተናዎቹን እየተቋቋምን ለአስር ዓመታት በተዘጋጀው መሪ ዕቅድ መሠረት ተግተን እንሠራለን ብለዋል።

ውይይቱም ሆነ ሥልጠናው ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጀምሮ እስከ አጥቢያ ድረስ አጠናክረን እንቀጥላለን ያሉት የመምሪያው ሐላፊ ለሥራው መነሣሣት ምክንያት የሆነው ቀደም ሲል አባቶቻችን ያደራጁትን መዋቅር እንደገና ወደቀድሞው አሠራር በመመለስ አጠናክረን ለመቀጠል ነው ብለዋል።የውይይቱና የሥልጠናው ተሳታፊዎችም በበኩላቸው እንደገለጹት በመምሪያው ተዘጋጅቶ የቀረበው ቀጣይ የሥራ ተግባራት ዕቅድ ችግሮችን የሚያስወግድ የ ቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ የሚያፋጥን ስብከተ ወንጌልን የሚያጠናክር በመሆኑ በቋንቋዎች ጨምር ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባዋል ብለዋል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ Link to: የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ Link to: “ደን(ዕጽዋት )ለምድራችን የደም ሥርና ልብሷ ነው።ስለሆነም ምድራችን ስሯ ተቆርጦ ሕይወቷን እንዳታጣ የመጠቅና የመንከባከብ ኃላፊነት የሰው ልጆች በመሆኑ ደኖቻችንን በመንከባከብ ኃላፊነታችንን እንወጣ።” Link to: “ደን(ዕጽዋት )ለምድራችን የደም ሥርና ልብሷ ነው።ስለሆነም ምድራችን ስሯ ተቆርጦ ሕይወቷን እንዳታጣ የመጠቅና የመንከባከብ ኃላፊነት የሰው ልጆች በመሆኑ ደኖቻችንን በመንከባከብ ኃላፊነታችንን እንወጣ።” “ደን(ዕጽዋት )ለምድራችን የደም ሥርና ልብሷ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top