የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርከ

October 23, 2023

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

•ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት
ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ
ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
•ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና
ጸሐፊ እና በሰሜን አሜሪካ የኒዮርክ እና
አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
•ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ
አባላት፤
ሁሉንም ጠብቆ የሚያስጠብቅ እግዚአብሔር አምላካችን ከተሠማራንበት የጥበቃ ስፍራችን አሰባስቦ በደሙ ስለዋጃት ቅድስት ቤተክርስቲያን እንድንመክር ስለፈቀደልን ምስጋና ለእሱ እናቀርባለን፣ እናንተም እንኳን ደኅና መጣችሁ ለማለት እንወዳለን፡፡
“ወዘእንበለዝ ብዙኅ ባዕድ ዘረከበኒ ኲሎ አሚረ እንዘ እኄሊ ቤተ ክርስቲያናት፡- የቀረውንም ነገር ሳልቈጥር ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ሐሳብ ነው” (2ኛ ቆሮ 11፦28)
ከዚህ ጥቅስ እንደምናስተውለው ከስራ ሁሉ የሚያስጨንቅ ተግባር የቤተ ክርስቲያን ነገር እንደሆነ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በሚገባ አስቀምጦአል፡፡ እርግጥ ነው ሌሎች የሚያስጨንቁ ችግሮች በዓለም አሉ  ግን ሌሎቹ ለጊዜውም ቢሆን ባላቸው ማቴሪያላዊ ኃይል ማስታገሥ ይችላሉ፡፡ ቤተክርስቲያን ግን ከመንፈስ ቅዱስ ከተሰጠ ረቂቅ ኃይለ መዊዕ በቀር ሌላ ማቴሪያላዊ ኃይል የላትም አይፈቀድላትምም፡፡
ይሁን እንጂ ከኃይል ሁሉ የበለጠ ኃይል እንዳለን ጌታችን ነግሮናል እኛም እናውቀዋለን፡፡ ነገር ግን የኛ ድክመት ኃይሉ እንደሚፈለገው እንዳይሰራ ያደርገዋል ይህም እውነት ነው የተሰጠን ኃይል በእኛ ድክመት የተቀዛቀዘ ቢመስልም የማይሸነፍ ነውና ኃይላችንን አውቀን ካልተጠቀምንበት እኛንም ጭምር ቀጥቶ የበላይ አሸናፊነቱን ያረጋግጣል ይህም የታየ እውነት ነው፡፡
ስለሆነም ሐዋርያው እንዳለው በውስጣችን ያለው ኃይል አቀጣጥለን ሙሉ በሙሉ መጠቀም እንችል ዘንድ ራሳችንን ክደን ለእግዚአብሔር ክብርና ለቤተክርስቲያኑ ተልእኮ በአንድነት መቆም የግድ ይላል፡፡
ቤተ ክርስቲያን ያለ መከራ አልኖረችም ለወደፊትም ከዚያ የተለየ ዕድል አትጠብቅም፡፡ ለምን ቢባል ጥበበኛው ሰሎሞን እንደነገረን “በእሾኽ መካከል ያበበች የሃይማኖት አበባ” ናትና ነው፡፡ ጌታችንም ስለ ስሜ በሁሉም ዘንድ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ ያሳድዱአችኋል፣ይገርፉአችኋል፣ ይገድሉአችሁማል ብሎ ዕቅጩን ነግሮናል፡፡
ዓለም እንደ ካሁኑ በፊት አሁንም በእሾኽነትዋ ቤተ ክርስቲያንን እየወጋች ነው ታዲያ ከመጽናት በቀር ከኛ ሌላ ምን ይጠበቃል?
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ወኤጲስ ቆጶሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!!
እኛ ያለንበት የመልክዐ ምድር አቀማመጥ እጅግ ፈታኝ ነው፡፡ ዓለም እኛን ለመጥቀም ሳይሆን ለራሱ ሲል የሚቀራመተው አካባቢ ነው፡፡ ለዚያ ሲባል የደረሰብንም ጫና ምን ያህል እንደሆነ የምንስተው አይደለም እኛም አንድነታችንንና ወንድማማችነታችንን አጽንተን መቆም ባለመቻላችን ለአደጋው ይበልጥ ተጋላጭ ሆነናል፡፡
ሕዝብ ተጐዳ ማለት ቤተክርስቲያን ተጐዳች ማለት እንደሆነ አንርሳው ቤተክርስቲያን ማለት በዋናነት ሕዝበ ክርስቲያን ነውና፡፡ ያለንበት አካባቢ ለልዩ ልዩ ጥቃት የተጋለጠ ሆኖ ሳለ ቤተክርስቲያናችን ለሁለት ሺሕ ዓመታት ያህል ብቻ ለብቻ ሆና በሃይማኖተ ክርስትና መዝለቋ እጅግ የሚያስደንቅ መሆኑን እናስታውስ፡፡
ይህ የሚያሳየው የቀደምት አባቶቻችን ጽንዐ ሃይማኖትና ጥንካሬ ስለሆነ ሳናመሰግናቸው ብናልፍ ትልቅ ኃጢአት ይሆንብናል እነሱን ማመስገንም በቃላት ብቻ አይሆንም፡፡
እነሱ የሰሩትን በመጠበቅና በመድገምም እንጂ ለዚህ ተልእኮ ይህ ጉባኤ ኃላፊነት አለበትና ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት ይኖርበታል፡፡
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ወኤጲስ ቆጶሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!!
ከሁኔታዎች በትክክል መገንዘብ እንደሚቻለው ቤተክርስቲያናችን ከሚተቻት ይልቅ የሚወዳት ይበልጣል  በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉ ፈላጊዎቿ ብዙ ናቸው፡፡ ለዚህ ተጠቃሽ የሚሆኑን በሀገር ውስጥ የሚገኙ ልዩ ልዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች፣ እንደዚሁም በአፍሪካና በላቲን አሜሪካ የሚገኙ ሕዝቦች ናቸው፡፡ ለነዚህ ሕዝቦች ፈጣንና ዘላቂነት ያለው ግብረ መልስ ከዚህ ጉባኤ ይጠበቃል ይህ በቀጣዮቹ ዓመታት በመሪ ዕቅዱ መሠረት በስፋት የምንሰራው ስራ ይሆናል፡፡
ቤተክርስቲያን በዓሥር ሚሊዮኖች የሚቈጠሩ ተከታዮች በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር ያሏት በመሆኗ የሀብት ዕጥረት ያጋጥማታል ተብሎ አይጠረጠርም፡፡ ምክንያቱም ትልቁ ሀብት ሰው ስለሆነ ሰውን በቃለ ቅዱስ ወንጌል በሚገባ ከገነባች፣ አስተዳደርዋና የሀብት አያያዟ በትክክልና በሓቅ ጠብቃ ለሚገባው የሃይማኖት ተልእኮ ለማዋል የሚያስችል አሰራር ከዘረጋች  ይህንንም በምእመናን አእምሮና ዓይን ከተረጋገጠ እንኳን ለገንዘቡ ለሕይወቱ የማይሳሳ ምእመን እንዳላት ሁላችንም እናውቃለን፡፡ ታድያ ሀብት ማለት ይህ አይደለምን? አሁን መስራት ያለብንስ ይህ ሀብት በትክክል መጠበቁ ላይ አይደለምን?
ይህም በቀጣዩ ዓመት በስፋት የሚሰራበት ይሆናል  የዕቅበተ ንዋይ፣ የዕቅበተ ሃይማኖት፣ የሥልጠናና ትምህርት፣ የገዳማትና ቱሪዝም፣ የምርትና የደን ሀብት፣ የፋይናንሱ ሴክተርና የስብከተ ወንጌሉ ተልእኮ ዘመኑ በሚጠይቀው የአመራርና የአሰራር ጥበብና ስልት እየታገዝን፣ ሕዝባችንንም ከጎናችን እያሰለፍን የምንሰራበት ጊዜው አሁን ነው፡፡
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ወኤጲስ ቆጶሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!!
ለጀመርናቸውና ለወደፊት ለምንጀምራቸው የመልካም አስተዳደርና የልማት ስራዎች ዋስትና እንደሚያስፈልጋቸው እሙን ነው፡፡ የስራዎቻችን ዋስትናም በሀገርና በቤተክርስቲያን ፍጹም የሆነ ሰላምና አንድነት መኖር ነው፡፡ በመሆኑም የጠማንን ሰላምና አንድነት መልሶ ለማምጣት የቤተክርስቲያን ኃይል የአንበሳውን ድርሻ እንደሚወስድ ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ ሆኖም የቤተክርስቲያን የሰላም ጉዞ ከማንኛውም ወገንተኝነት በጸዳ፣ ማእከሉና ዓላማው የሀገርና የቤተክርስቲያንን አንድነት ብቻ መሠረት ያደረገ መሆን ይገባዋል
ከዚህ አንጻር በሀገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን በቤተክርስቲያናችንም እንከን የለሽ አንድነት እንዲረጋገጥ በብርቱ መስራት ይኖርብናል፡፡ አኲርፈው የተለዩትን በጠባይ ወደ እኛ እናምጣቸው እኛም ኲርፊያን ከሚያስከትል ድርጊት እንራቅ በአንድነት፣ በእኩልነትና በጋራ ሆነን ታላቋን ቤተክርስቲያን እንሰብስብ፣ እናገልግል፣ እንምራ፣ እንጠብቅ፡፡
ለዚህም ሙሉ ዝግጅት እናድርግ የዕለት ተዕለት ስራችን የቤተ ክርስቲያንን ጭንቀት የሚያቃልል ይሁን ይህ ከሆነ ቤተ ክርስቲያንን ያለምንም ጥርጥር በዕድገት ጐዳና ወደፊት እናሻግራለን፡፡
በመጨረሻም
የታላቋን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን መርምሮ ገምግሞና አጥንቶ ችግር ፈቺ ውሳኔን የመስጠት ኃላፊነት ያለው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተከፈተ መሆኑን በቤተክርቲያን ስም እናበስራለን፡፡ እግዚአብሔር የተባረከና የተቀደሰ ጉባኤ ያድርግልን!

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን፡፡
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓመተ ምሕረት
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የ፵፪ ኛው ዓለምአቀፍ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ስኬቶች፤ Link to: የ፵፪ ኛው ዓለምአቀፍ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ስኬቶች፤ የ፵፪ ኛው ዓለምአቀፍ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ... Link to: የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ አጀንዳ አርቃቂ ብፁዓን አባቶችን ሰየመ። Link to: የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ አጀንዳ አርቃቂ ብፁዓን አባቶችን ሰየመ። የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ አጀንዳ አርቃቂ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top