ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች
ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙሃን ሥርዓት ድርጅት(EOTC TV) ለሥራ አፈጻጸሙ የሚያግዙትን ቁሳቁስ በማማላት ላይ ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙሃን ሥርጭት ድርጅት EOTC TV ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ በሚዲያው ዘርፍ ብቁና ተመራጭ የሚያደረጉትን ተግባራት በማከናወን ላይ ይገኛል። ለዚህም ራሱን በሰለጠነ የሰው ኃይልና ቁሳቁስ በማደራጀት የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት የሚያስችሉትን ተግባራት በትጋት በማከናወን አሁን የሚገኝበት ቁመና ላይ ደርሷል።
፵፪ ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በተመረጡ አሥር የውይይት ነጥቦች ዙሪያ ውይይት እየተደረገ ይገኛል::
በዚህ የቡድን ውይይት የሚነሱ ነጥቦች ተጨምቀው በምልዓት ውይይት ከተደረገባቸው በኋላ ማጠቃለያ ተሰጥቶባቸውና የተነሱት ነጥቦች በአቋም መግለጫው ተካተው ለቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የሚቀርቡ ይሆናል።
፵፪ ኛው ዓለምአቀፍ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ
ለ፵፪ ኛ ጊዜ የሚካሔደው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዓለም አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የተዋጣለት፣የተሳካና ውጤታማ በሆነ መልኩ መከናወን ይችል ዘንድ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎቹ በሚገባ ታቅደው፣ ለእያንዳንዱ ተግባር አስፈጻሚና ፈጻሚ አካል ተቀምጦለት የተከወነ ከመሆኑም በላይ የእያንዳንዱ ኮሚቴ የሥራ አፈጻጸምና አጠቃላይ የቅድመ ዝግጅት ሥራው አፈጻጸም በብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሚመሩት አስተዳደር ጉባኤ ተገምግሞ ማስተካከያ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ከተስተካከሉና ከታረሙ በኋላ ወደ ተግባር እንዲለወጡ ተደርጓል፤ ይህም በመደረጉ እያንዳንዱ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ያማረና የተዋበ እንዲሆን ማድረግከመቻሉም በላይ በአፈጻጸም ደረጃም ውጤት የተመዘገበበት መሆን ችሏል።
ለሰ/ት/ቤቶች መማሪያነት የተዘጋጀውን ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ ለማድረግ የሁሉም ርብርብ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ።
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በኩል ተዘጋጅቶ ወደ እንቅሰቃሴ እየገባ በሚገኘው የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ዙሪያ ለ አጠቃላይ ዓለም አቀፍ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ተሳታፊዎች ማብራሪያ ቀርቧል።
ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም (ልጅ ያሬድ) ማረሚያ ቤት እንዲወርድ ታዘዘ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም ባልቻ በቅጽል ስሙ (ልጅ ያሬድ) በቀረበበት ተደራራቢ ክስ ማረሚያ ቤት እንዲወርድ ታዘዘ።
“የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ከጠፋንበት አገኘችን” ትውልደ አሜሪካዊው ካህን
በዛሬው የሪፖርት ቀን ከሀገር ውስጥ አኅጉረ ስብከቶች በተጨማሪ ከኢትዮጵያ ውጭ ያሉ አኅጉረ ስብከቶች ሪፖርታቸውን ማቅረብ ጀምረዋል። በጉባኤው ላይ ከቀረቡት ሪፖርቶች መካከል አንዱ የሆነው የኒዮርክ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሪፖርት ሲሆን ያቀረቡት ትውልደ አሜሪካዊው መልአከ ገነት ተስፋ ኢየሱስ ናቸው።
በራያና አካባቢው የሚገኙ ስድስት ወረዳዎችን እንዲያስተባብር የተቋቋመው ጽሕፈት ቤት በ፵፪ኛው ዓለምአቀፍ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርቱን አቀረበ።
በሐምሌ ወር ፳፻ ፲ወ ፭ ዓ.ም አስቸኳይ ጉባኤውን ያካሄደው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በራያና አካባቢው ከሚገኙ ስድስት ወረዳዎች የቀረበለትን ጊዜያዊ ጽሕፈት ቤት ይቋቋምልንና የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ እንዲመሩን ይፈቀድልን በማለት ያቀረበውን ጥያቄ በመቀበል ችግሩ እስከሚፈታ ድረስ በአካባቢው የሚገኙ ምዕመናን አገልግሎት ማግኘት ይችሉ ዘንድ ጽሕፈት ቤቱ እንዲቋቋም ውሳኔ ማስተላለፉን ተከትሎ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤቱ ተቋቁሞ ፣ቢሮ ተከራይቶና ኃላፊዎች ተመድበውለት ሥራውን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱሳት መጻሕፍትን በአእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን የፈጠራ ባለቤትነት መብት ተመዘገበ።
የምዝገባ ሰርተፍኬት የተሰጠው ለስምንቱ ብሔረ ኦሪት ከዘፍጥረት እስከ መጽሐፈ ሩት ላለው ነጠላ ትርጉም መሆኑ ታውቋል።
ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማዕከል በ፵፪ ኛው አጠቃላይ ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤላይ ያቀረበው ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት የሚከተለው ነው።
ማኅበረ ቅዱሳን በ፳፻፲፭ ዓ.ም ካከናወናቸው መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቶች ውስጥ የሚከተሉት ዐበይት ተግባራት ተጠቃሽ ናቸው፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት 42ኛ ዓመት የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ያስተላለፋት ሙሉ የመክፈቻ መልእክት
ጸዊረ መስቀል ምንም የመረረ ቢሆንም ተሸንፎ ግን አያውቅም ነገረ መስቀል በአሸናፊነት እንጂ በተሸናፊነት አይታወቅምና ነው ቅዱሳን ሐዋርያት ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ መግባት አለብን ሲሉ የመከራ መስቀል ዓጸፋ አሸናፊነትና መዳን መሆኑን ስለሚያውቁ ነው በሀገራችንም ሆነ በመላው ዓለም ዙሪያ ያሉ ክርስቲያኖች የተለያዩ ጸዋትወ መከራዎችን በመቀበል የሚገኙት ከመንፈስ ቅዱስ ኃይልና ከሐዋርያት ተጋድሎ ባገኙት ውርስ ነው፡፡