የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የገዳማት አበ ምኔቶች እና እመ ምኔቶች በቤ ተክርስቲያችን ሁለንተናዊ ጉዳዮች ላይ እየመከሩ ነው፡፡

June 11, 2024

ሰኔ 5 ቀን 2016 ዓ/ም አዲስ አበባ

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ገዳማት አስተዳደር መምሪያ ያዘጋጀውና በሀገራችን አራቱም ማዕዘናት የሚገኙ ገዳማት አበ ምኔቶች እና እመ ምኔቶች የሚሳተፉበት የውይይትና የምክክር ጉባኤ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በሚገኘው ጽርሐ-ተዋሕዶ አዳራሽ በመካሄድ ላይ ነው፡፡

ጉባኤው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ጸሎትና ቃለ በረከት የተጀመረ ሲሆን ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተዘጋጀው የውይይትና የምክክር መድረክ አስፈላጊነትኛ ጠቃሚነት ዙሪያ የሥራ መመሪያና አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ መምሪያውም እንዲህ ዐይነት ለሀገርና ለቤተክርስቲያን የሚጠቅም ጉባኤ በማዘጋጀቱ ሊመሰገን እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ገዳማት አስተዳደር መምሪያ በዓመቱ ካቀዳቸውና ካከናወናቸው ተግባራት መካከል አንዱ በሆነው በዚህ ሀገር አቀፍ የውይትና የምክክር መድረክ ከቀድሞው ለየት ባለ መልኩ ከገዳማት አበ ምኔቶች በተጨማሪ እመ ምኔቶች እንዲካተቱ ከማድረጉም በላይ የየአህጉረ ስብከቱ የገዳማት አስተዳደር ክፍል ኃላፊዎች እና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚገኙ ገዳማት አስተዳዳሪዎችም እዲሳተፉ አድርጓል፡፡

በጉባኤው ለገዳማውያኑ የውይይትና የምክክር መነሻ የሚሆኑ ጥናታዊ ጽሑፎች በቤተ ክርስቲያናችን የሚቀርቡ ሲሆን ገዳማውያን አባቶችና እናቶችም በሚቀርቡት ጥናታዊ ጽሑፎች መነሻነት የሚወወያዩ ይሆናል፡፡ መምሪያው ያዘጋጀው ይህ የውይይትና የምክክር ጉባኤ ስለ ሀገር ሰላም የሚጸለይበት ገዳማውያን ስለ አሐቲ ቤተ ክርስቲያን አጥብቀው የሚመክሩበትና መልእክታቸውንም በመላው ዓለም ለሚገኙ የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን ልጆች እና ለቤተ ክርስቲያናችን ወዳጆች የሚያስተላልፉበት እንደሚሆን የመምሪያው ዋና ኃላፊ መጋቤ ካህናት ቆሞስ አባ ሀብተጊዮርጊስ አሥራት ገልጸዋል፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • የድሬዳዋ ሳባ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ያስገኘባው ባለ ሦስት ወለል ሁለገብ ሕንጻ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጸሎተ ቡራኬ በዛሬው ዕለት ተመረቋል።
  • የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ሕንጻ ቤተክርስቲያን ዕድሳት ተጠናቆ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው ተባረከ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ ወደ ቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ተጓዘ።
  • አሐዱ ባንክ ላደረገው ሁለተናዊ እገዛ በቋሚ ሲኖዶስ የእውቅናና የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበረከተለት።
  • የመቱ ፈለገ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ የመጀመሪያውን ዙር እጩ መምህራን በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስመረቀ

Archives

  • July 2026
  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የኢኦቴቤ መገናኛ ብዙሃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት የቀጥታ የሳተላይት ቴሌቪዥን ሥርጭት ለመጀመር ባከናወነው ተግባር ለተሳተፉ አካላት የምስጋና ፕሮግራም እያካሄደ ይገኛል። Link to: የኢኦቴቤ መገናኛ ብዙሃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት የቀጥታ የሳተላይት ቴሌቪዥን ሥርጭት ለመጀመር ባከናወነው ተግባር ለተሳተፉ አካላት የምስጋና ፕሮግራም እያካሄደ ይገኛል። የኢኦቴቤ መገናኛ ብዙሃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት... Link to: ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ መንፈሳዊ ማኅበር ቅዱስ ሲኖስ ያወጣውን የማኅበራት ምዝገባ መስፈርት አሟልቶ በመገኘቱ የዕውቅና የምስክር ወረቀት ተሰጠው። Link to: ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ መንፈሳዊ ማኅበር ቅዱስ ሲኖስ ያወጣውን የማኅበራት ምዝገባ መስፈርት አሟልቶ በመገኘቱ የዕውቅና የምስክር ወረቀት ተሰጠው። ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ መንፈሳዊ ማኅበር ቅዱስ ሲኖስ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top