የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ቅዱስ ፓትርያርኩ በደቡብ አፍሪካ ጁሐንስበርግ ጽርሐ ጽዮንመድኀኔዓለም ካቴድራል የተመሰረተበትን ፳፭ኛ ዓመት በዓል አከበሩ።

May 14, 2024

ግንቦት ፬ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ/ም
“””””””””””””””””””””””””””
ደቡብ አፍሪካ- ጁሐንስበርግ
==================

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፣ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት፣ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የዳውሮ-ኮንታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ በደቡብ አፍሪካ ጁሐንስበርግ ጽርሐ ጽዮን መድኀኔዓለም ካቴድራል የተመሰረተበትን ፳፭ኛ ዓመት በዓል ለማክበር በደቡብ አፍሪካ የተለያዩ ግዛቶች የሚገኙ አብያተክር
ስቲያናትና ምዕመናንን ለመጎብኘትና ለመባረክ ደቡብ አፍሪካ ጁሐንስበርግ መግባታቸው ይታወሳል።

ቅዱስነታቸው በዛሬው እለት በደቡብ አፍሪካ የጆሐንስበርግ መንበረ ጵጵስና ጽርሐ ጽዮን መድኃኔዓለም ካቴድራል በመገኘትም ካቴድራሉ የተመሰረተበትን ፳፭ኛ ዓመት በዐልን አክብረዋል።

በዓሉ በማኅሌት፣ቅዳሴ፣ በዝማሬና በልዩልዩ መንፈሳዊ መርሐ ግብሮች የተከበረ ሲሆን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በኢትዮጵያ የግሪክ ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስና የደቡብ አፍሪካ ዜግነት ያላቸው ኦርቶዶክሳዊያን ካህናትም የበዓሉ ታዳሚዎች ሲሆኑ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ምዕመናንና ምዕመናትም ተገኝተዋል።

በዚሁ ጊዜ በሀገረ ስብከቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት በሪፖርት ቀርበዋል።በሪፖርቱም በሀገረ ስብከቱ ሀገሩንና ቦታውን የሚመጥን የአስተዳደር ሥርዓት በመዘርጋቱን፣ ሕዝበ ክርስቲያኑ መንፈሳዊ ዕወቀቱ እንዲጎለብት፣ በሃይማኖቱ እንዲጸና፣ተተኪ ወጣቶች መንፈሳዊ ዕውቀትን እንዲገበዩ፣ የሚያደርጉ ተግባራት መከናወናቸውን፣ አዳዲስ አብያተክርስቲያናት በአገሪቱ በአራቱም ማዕዘን እንዲተከሉና ስብከተወንጌል እንዲስፋፋ መደረጉን የሚገልጽ ሪፖርት ቀርቧል። በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ደቡብ አፍሪካዊያን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ካህናትም የእንኳን ደህና መጣችሁና የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመቀጠልም ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በኢትዮጵያ የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት መልዕክት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና የግሪክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የረጅም ጊዜ ግንኙነት እንዳላቸው ገልጸው ቅዱስ አባታችን በደቡብ አፍሪካ በመገኘታቸው የተሰማቸውን ደስታ በመግለጽ ለቅዱስነታቸው የክብር ስጦታ አበርክተዋል።

በብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የዳውሮ-ኮንታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ትንሣኤ ሙታንን በተመለከተ ሰፊ ትምህርተ ወንጌል የተሰጠ ሲሆን ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ በደቡብ ና ደቡብ ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት የተሰሩ ዋናዋና ሥራዎች፣ ባለፉት አራት ዓመታት የተተከሉ አዳዲስ አብያተክርስቲያናትና ወደፊት የሚተከቱ አዳዲስ አብያተክርስቲያናትን የሥራ አፈጻጸምን በተመለከተ አጭር ሪፖርት አቅርበው ቅዱስነታቸው ለበዓሉ ታዳሚዎች ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ እንዲሰጡ ጋብዘዋል።

በመጨረሻም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፒትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱምጨወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ፦ እግዚአብሔርን እንድናመልክ ቅድስት እርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ስላሰባሰበችን ክብር ምስጋና ለእግዚአብሔር ይግባው፤ካሉ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ የዚህን የጁሐንስበርግ ጽርሐ ጽዮን መድኀኔዓለም ካቴድራልን ሃያ አምስተኛ ዓመት በዓል በጋራ እንድናከብር ከያለንበት ስለሰበሰበንና በጋራ እንድናከብር ስላደረገን አሁንም ክብር ምስጋና ይግባው።ብለዋል።

ይህን ካቴድራል በዚህ መልኩ አሳምራችሁና አስውባችሁ በመሥራት ለአገልግሎት ምቹ ያደረጋችሁና በዚህ የተቀደሰ ሥራ በልዩልዩ መልኩ በመሰማራት አስተዋጽኦ ያደረጋችሁ ልጆቻችን ሁሉ ምስጋና ይገባችኋል።ያሉት ቅዱስ ፓትርያርኩ የቤተክርስቲያኑ ቅጽረ ጊቢ ጠባብ ስለሆነ ወደፊት ፓርኪንግ ያለው ሕዝበ ክርስቲያኑ አየር እየተቀበለ ፣ኡደት እየተደረገ በዓል የሚከበርበት ቤተክርስቲያን በአጭር ጊዜ ሰርታችሁ ለአገልግሎት እንድታበቁት አደራ እንላለን በማለት ቃለ ቡራኬና ቃለ ምዕዳን በመስጠት የበዓሉ ፍጻሜ ሆኗል።

ከቅዱስነታቸው ቃለምዕዳንና ቃለ ቡራኬ ቀደም ብሎም ለቅዱስነታቸው፣ለብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ፣ ለብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ለቤፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በኢትዮጵያ የግሪክ ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ፣ በጁሐንስበርግ ጽርሐ ጽዮን መድኀኔዓለም ካቴድራል የተከናወኑ የልማት ሥራዎችን በገንዘባቸው፣ በእውቀታቸውና በጉልበታቸው በመደገፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ወገኖች ሀገረ ስብከቱ ያዘጋጀላቸው ሽልማት ተበርክቷል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ አርሲ-አቦምሳ ወረዳ ተገኝቶ ምዕመናንን አጽናና ጊዜያዊ ርዳታም አበረከተ።
  • “በአርሲ የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን እንሠራለን” የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች
  • ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በሀገረ ስብከቱ ለካህናት የሚሰጠውን ሥልጠና በጸሎትና በቡራኬ አስጀመሩ።
  • ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ተገኝተው የተጎዱ ወገኖችን የሚያጽናኑ በፁዐን አባቶችን መደበ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን የልዑካን ቡድን ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሰላም ሚኒስቴርና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያየ።

Archives

  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: “የማይኾን ጸጸት እንዳንጸጸት በሰዓቱ እና በጊዜው ንስሐ እንግባ” ብጹዕ አቡነ አብርሃም ፤ Link to: “የማይኾን ጸጸት እንዳንጸጸት በሰዓቱ እና በጊዜው ንስሐ እንግባ” ብጹዕ አቡነ አብርሃም ፤ “የማይኾን ጸጸት እንዳንጸጸት በሰዓቱ እና በጊዜው... Link to: የቤተክርስቲያናችን ሕዝብ ግንኙነት ከላይ እስከ  ታች ተናቦና ተሳስሮ መሰራት ይኖርበታል። Link to: የቤተክርስቲያናችን ሕዝብ ግንኙነት ከላይ እስከ  ታች ተናቦና ተሳስሮ መሰራት ይኖርበታል። የቤተክርስቲያናችን ሕዝብ ግንኙነት ከላይ እስከ ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top