ልማት በቤተ ክርስቲያን
ልዮ ዕትም መጽሔት
ይህ ”ልማት በቤተክርስቲያን“ የተሰኘ ልዮ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አዘጋጅነት ‹‹ኦርቶዶክሳዊ ብዙኃን መገናኛ ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን›› በሚል መሪ ቃል በተደረገው የሥልጠና፣ ውይይትና የምክክር መርሐ-ግብር በተሳተፍን የቤተ ክርስቲያን ልጆች የቀረበ የአቋም መግለጫ፤
ሚያዝያ 7 ቀን 2016 ዓ/ም
ኦርቶዶክሳውያን ብዙኃን መገናኛ ተቋማትና ማኅበራዊ ሚዲያዎች ሐሰተኛ ወሬ ባለመቀበል እና ባለማስተላለፍ ኃላፊነታቸውን ሊውጡ እንደሚገባ ብፁዕ አቡነ አብርሃም አሳሰቡ።
“ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን በጣስ መልኩ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን እና ሥርዓተ አምልኮ በዲጂታል ሚዲያ የሚያስተላልፉ አገልጋዮች እና ሌሎች የማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ከድርጊታቸው መቆጠብ ይገባቸዋል” ብፁዕ አቡነ አብርሃም
ኦርቶዶክሳውያን ብዙኀን መገናኛ ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
የኢ.ኦ.ተ.ቤ. ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ “ኦሮቶዶክሳዊያን ብዙኀን መገናኛ ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን” በሚል ርዕስ በዛሬው ዕለት የሥልጠና፣ የምክክርና የውይይት መድረክ በጁፒተር ኢንተርናሽናል ሆቴል አካሂዷል።
ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል የደምቢ ደሎ ደ/ጸሐይ መድኃኔዓለም ካቴድራልን ቅዳሴ ቤት አከበሩ።
ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል የቄለም ወለጋ፣ የጋምቤላ ክልልና ደቡብ ሱዳን፣ የቤ/ጉሙዝ አሶሳ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የሰላምና የልማት አምባሳደር በዛሬው ዕለት በ27/07/2016 በደምቢ ዶሎ ደ/ጸሐይ መድኃኔዓለም ካቴድራል በመገኘት የታደሰውን ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን በመባረክ፣ ቅዳሴ ቤቱን አክብረዋል።
የብፁዕ አቡነ ሩፋኤል ሐዋርያዊ ጉዞ
ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል የቄለም ወለጋ፣ የጋምቤላ ክልልና ደቡብ ሱዳን፣ የቤ/ጉሙዝ አሶሳ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የሰላምና የልማት አምባሳደር የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በዛሬው ዕለት (26/07/2016) ሐዋርያዊና መንፈሳዊ ጉዞአቸውን ከአዲስ አበባ ወደ ቄለም ወለጋ ሀገረ ስብከት ደምቢ ዶሎ በማድረግ ላይ እንዳሉ በዳሌ ሰዲ ወረዳ ቤተ ክህነት ጫሞ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
በቁልቢና አካባቢው ልዩልዩ የልማት ሥራዎች እንዲከናወኑ ውሳኔ ተለይተው ተላልፏል።
መጋቢት ፳፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
የጽርሐ ጽዮን ዘተዋሕዶ የሐዋርያት አንድነት ኑሮ ማኅበር በማሰልጠኛ ማዕከሉ ያስተማራቸውን ተማሪዎች አስመረቀ ።
የጽርሐጽዮን ዘተዋሕዶ የሐዋርያት አንድነት ኑሮ ማኅበር የሰባክያነ ወንጌልና የአብነት ትምህርት ማሠልጠኛ ለቤተክርስቲያን ዘቢብ ጧፍ ጥላ ሻማ ብቻ ሳይሆን ሰውንም እንስጥ በሚል መሪ ቃል የተቋቋመ ማሰልጠኛ ማዕከል እንደመሆኑ መጠን ከልዩ ልዩ አህጉረ ስብከቶች የተወጣጡ ሰልጣኞችን በየቋንቋቸው አሰልጥኖ አስመርቋል።
የመልአከ ፀሐይ መኰንን ደስታ ግብአተ መሬት ተፈጸመ።
ረጅሙን የሕይወት ዘመናቸውን ቤተክርስቲያንን በሀገር ውስጥና በሰሜን አሜሪካ በቅንነትና በትህና ሲያገለግሉ የኖሩት የመልአከ ፀሐይ መኰንን ደስታ ጸሎተ ፍትሐትና ሽኝት ከልጅነት እስከ ዕውቀት ባገለገሉበት በአዲስ አበባ ገነተ ኢየሱስ ገነተ ማርያም ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።
ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በአሮጌው ቄራና በጠቅላይ ቤተክህነት በግንባታ ላይ የሚገኙትን ሕንጻዎች የሥራ አፈጻጸም ተዘዋውረው ተመለከቱ።
መጋቢት ፲፭ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
የአመራር ብቃትን ለማሳደግና ዘመኑን የዋጀ የአሰራር ሥርዓትን ለመዘርጋት የሚያስችል የምክክር ጉባኤ በጠቅላይ ቤተክህነት በመካሔድ ላይ ነው።
መጋቢት ፲ቀን፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም