ልማት በቤተ ክርስቲያን
ልዮ ዕትም መጽሔት
ይህ ”ልማት በቤተክርስቲያን“ የተሰኘ ልዮ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።
ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት መፍትሔ ሊሰጥባቸው ይገባል ያላቸውን በ13 ነጥቦች የተዘረዘሩ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በሀገረ ስብከቱ በኩል መፍትሔ እንዲሰጣቸው ውሳኔ አስተላለፈ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጋር ባደረገው ውይይት በሀገረ ስብከቱ በኩል የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በተመለከተ በተደረገው የጋራ ውይይት በሀገረ ስብከቱ የሚስተዋሉትን ዋናዋና ችግሮች መቅረፍ ይቻል ዘንድ በጠቅላይ ቤተክህነት በኩል ተለይተው የሚታወቁት ዋናዋና ነጥቦች ለሀገረ ስብከቱ እንዲደርሰው ተደርጎ መፍትሔ እንዲሰጥበት የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሔኖክ በጉባኤው ወቅት በሰጡት ማጠቃለያ ሀሳብ ላይ በገለጹት መሰረት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት አስተዳደር ጉባኤ ኅዳር 24ቀን2016ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ ሀገረ ስብከቱ በኩል በአፋጣኝ ምላሽ ሊያገኙ ይገባቸዋል ያላቸውን 13 ነጥቦችን በመለየት ለሀገረ ስብከቱ እንዲደርሰውና ከበዛ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለተጠቀሱት የመልካም አስተዳደር ችግሮች ምላሽ እንዲሰጥና የውሳኔውን መፈጸም አለመፈጸም በተመለከተም ተከታትለው የሚያስፈጽሙ ሦስት የመምሪያ ኃላፊዎችን መድቧል።
በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የተፈጸመውን ግድያ የጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር ጉባኤ አወገዘ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር ጉባኤ በዛሬው እለት ባደረገው መደበኛ ስብሰባ በምሥራቅ አርሲ አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ላይ የደረሰውን የሞት አደጋ በተመለከተ ኅዳር 24 ቀን 2016ዓ.ም ከሀገረ ስብከቱ በስልክና በደብዳቤ የደረሰውን መረጃ መነሻ በማድረግ ውይይት ካደረገ በኋላ ውሳኔ አስተላልፏል።
በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የተፈጸመውን ጥቃት በማስመልከት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የተሰጠ መግለጫ ፤
በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት በጥብቅ እናወግዛለን፤የጸጥታ ተቋማትም ጥቃቱን እንዲከላለሉ እንጠይቃለን።
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/አስተዳደር ጉባኤ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በኩል አስቸኳይ መፍትሔ ሊሰጣቸው ይገባል ያላቸውን ፲፪ ነጥቦችን የያዙ ውሳኔዎችን አስተላለፈ።
የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የመልካም አስተዳደር ችግሮችን አስመልክቶ የጋራ የውይይት መድረክ እንዲመቻችና በሚደረገው ውይይትም ችግሮችን በዝርዝር በመለየትና በመፈተሸ የመፍትሔ አቅጣጫ ማስቀመጥ እንዲቻል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጉባኤ ጥቅምት ፳፯ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም ውሳኔ ማስተላለፉ ይታወሳል።
ብፁዕ_ወቅዱስ ፓትርያርኩ የኅዳር ጽዮን በዓለ ንግሥ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም አከበሩ።
በየዓመቱ ኅዳር 21 ቀን በከፍተኛ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት የሚከበረውን የኅዳር ጽዮን በዓለ ንግሥ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ_ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፣ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የልዩ ልዩ የመምሪያ ኃላፊዎች ፣ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና በሽህ የሚቆጠሩ ምእመናን በተገኙበት ዛሬ ኅዳር 21 ቀን 2016 ዓ,ም በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያምገዳም በድምቀት ተከብሯል።
ያልተነበቡት አንቀጾች
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጥቅምት ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተዳደራዊ ችግሮችን በመቅረፍ ለሀገረ ስብከቱ የቤተክርስቲያናችንን ሕጎችና መመሪያዎችን መሰረት ያደረገ ራሱን የቻለ መተዳደሪያ ደንብ በባለሙያዎች እንዲዘጋጅለት በማድረግና ደንቡን መርምሮ በማጽደቅ ወደ በሥራ ላይ እንዲውል ውሳኔ መስጠቱ ይታወሳል።
የተዛባ መረጃ ለህዝብ በማድረስ የሚፈታ የመልካም አስተዳደር ችግር የለም።
በዛሬው ዕለት የጠቅላይ ቤተክህነትና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተዳደር ጉባኤ በጋራ ባደረጉት ስብሰባ በርካታ ጉዳዮች ተነስተው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።
፵፪ኛው የሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ተካሔደ።
የማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ፵፪ኛውን አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤውን አካሔደ።የሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባዔው ከመካሔዱ አንድ ቀን ቀደም ብሎም በሀገረ ስብከቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ታላቅ ጉባኤ መካሔዱን ከሀገረ ስብከቱ የደረሰን ዘገባ ያመለክታል።
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ቤተክህነት መሆኑን በመገንዘብ ሕግና መመሪያን አክብሮ እውነትና እውነተኝነትን መርሁ አድርጎ እንዲሰራ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አሳሰቡ።
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሚታዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በጋራ ለመፍታትና መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት የጠቅላይ ቤተክህነትና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአስተዳደር ጉባኤ አባላት በዛሬው እለት ባደረጉት የጋራ ጉባኤ ተስማሙ።
የጠቅላይ ቤተክህነትና የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት አስተዳደር ጉባዔ አባላት በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ የጋራ ጉባዔ በማድረግ ላይ ናቸው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተዳደር ጉባኤ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአስተዳደር ጉባኤ አባላት ጋር በሁለትዮሽ የአሰራር ሒደት፣በመልካም አስተዳደር፣በሕግ ፣ደንቦችና መመሪያዎች አከባበር በአጠቃላይ ሥራዎችን በተቋማዊ አሰራር ሒደት በማከናወን ዙሪያ የጋራ መድረክ ተዘጋጅቶ ውይይት እንዲደረግ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተክህነት አስተዳደር ጉባኤ ያስተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ዛሬ ኅዳር ፲፰ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ የጋራ ጉባኤ በማካሔድ ላይ ናቸው።