ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች

የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ አጀንዳ አርቃቂ ብፁዓን አባቶችን ሰየመ።

ከቅዱስነታቸው የመክፈቻ መልእክት በኋላም የመወያያ አጀንዳ ቀርጸው የሚያቀርቡ ሰባት ሊቃነ ጳጳሳትን ሰይሟል።

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርከ

የታላቋን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን መርምሮ ገምግሞና አጥንቶ ችግር ፈቺ ውሳኔን የመስጠት ኃላፊነት ያለው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተከፈተ መሆኑን በቤተክርቲያን ስም እናበስራለን፡፡ እግዚአብሔር የተባረከና የተቀደሰ ጉባኤ ያድርግልን!

የ፵፪ ኛው አጠቃላይ ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የተለያዩ የአቋም መግለጫ ነጥቦችን በማውጣት ተጠናቋል።

ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም የጀመረው የ፵፪ ኛው አጠቃላይ ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ለተከታታይ 5 ቀናት ያደረገውን ውይይት በዛሬው ዕለት አጠናቋል።

ቅዱስ ሲኖዶስ ለውጭ አሁጉረ ስብከት ወጥ የሆነ መመሪያ እንዲያወጣ ብፁዕ አቡነ ሙሴ ጠየቁ።

ብፁዕ አቡነ ሙሴ የምዕራብ አውስትራሊያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በ፵፪ኛው ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ የሀገረ ስብከታቸውን ሪፖርት አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙሃን ሥርዓት ድርጅት(EOTC TV) ለሥራ አፈጻጸሙ የሚያግዙትን ቁሳቁስ በማማላት ላይ ነው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙሃን ሥርጭት ድርጅት EOTC TV ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ በሚዲያው ዘርፍ ብቁና ተመራጭ የሚያደረጉትን ተግባራት በማከናወን ላይ ይገኛል። ለዚህም ራሱን በሰለጠነ የሰው ኃይልና ቁሳቁስ በማደራጀት የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት የሚያስችሉትን ተግባራት በትጋት በማከናወን አሁን የሚገኝበት ቁመና ላይ ደርሷል።

፵፪ ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በተመረጡ አሥር የውይይት ነጥቦች ዙሪያ ውይይት እየተደረገ ይገኛል::

በዚህ የቡድን ውይይት የሚነሱ ነጥቦች ተጨምቀው በምልዓት ውይይት ከተደረገባቸው በኋላ ማጠቃለያ ተሰጥቶባቸውና የተነሱት ነጥቦች በአቋም መግለጫው ተካተው ለቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የሚቀርቡ ይሆናል።

፵፪ ኛው ዓለምአቀፍ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ

ለ፵፪ ኛ ጊዜ የሚካሔደው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዓለም አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የተዋጣለት፣የተሳካና ውጤታማ በሆነ መልኩ መከናወን ይችል ዘንድ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎቹ በሚገባ ታቅደው፣ ለእያንዳንዱ ተግባር አስፈጻሚና ፈጻሚ አካል ተቀምጦለት የተከወነ ከመሆኑም በላይ የእያንዳንዱ ኮሚቴ የሥራ አፈጻጸምና አጠቃላይ የቅድመ ዝግጅት ሥራው አፈጻጸም በብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሚመሩት አስተዳደር ጉባኤ ተገምግሞ ማስተካከያ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ከተስተካከሉና ከታረሙ በኋላ ወደ ተግባር እንዲለወጡ ተደርጓል፤ ይህም በመደረጉ እያንዳንዱ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ያማረና የተዋበ እንዲሆን ማድረግከመቻሉም በላይ በአፈጻጸም ደረጃም ውጤት የተመዘገበበት መሆን ችሏል።

ለሰ/ት/ቤቶች መማሪያነት የተዘጋጀውን ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ ለማድረግ የሁሉም ርብርብ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ።

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በኩል ተዘጋጅቶ ወደ እንቅሰቃሴ እየገባ በሚገኘው የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ዙሪያ ለ አጠቃላይ ዓለም አቀፍ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ተሳታፊዎች ማብራሪያ ቀርቧል።

በፌስቡክ ያግኙን

የኅትመትና ሚዲያ ዋና ክፍል

ብፁዕ አቡነ አብርሃም

የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ

በሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ እና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ

ለውስጥ አገልግሎት

የኢሜይል አገልግሎት

ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን

ርእይ

ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት

ተልእኮ

  • የእግዚአብሔርን ቃል ለሰው ልጆች ሁሉ ማስተማርና ማዳረስ

  • ሰውን በሁለንተናዊ ሰብእናው ማገልገልና ማዳን

  • ሰውን ሁሉ በነገረ መለኮትና በነገረ ጥበብ ትምህርት በማልማት በመንፈሳዊም ሆነ በሥጋዊ ሕይወቱ የተሻለ ኑሮ እንዲኖረው ማድረግ

  • ጥራትና ብቃት፣ ፍትሐዊነትና እኩል ተደራሽነት ያለው መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ለሰው ሁሉ ማበርከት

  • የተለያዩ የልማት መርሀ ግብሮችን በመንደፍ ቤተ ክርስቲያንን በኢኮኖሚ ማበልጸግ

  • በቴክኖሎጂ ስልት የሚመራና አዋጭነቱ አስተማማኝ የሆነ የጠቅላላ ሀብት አስተዳደርና አጠቃቀም እንዲረጋገጥ ማድረግ

  • የሰው ልጆች ሁሉ እኩልነት፣ ሰላምና ፍትሕ፣ ፍቅርና ስምምነት እንዲጠበቅ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ

  • የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አሰራር ግልጽ፣ ለሁሉም ተደራሽና ችግር ፈቺ እንዲሆን ማድረግ

ዕሴቶች

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅሊናን የሚረታ፣ አእምሮን የሚመሥጥ፣ ከጥንተ ፍጥረት ተነሥቶ በዘመነ አበው በሕገ ልቡና፣ በዘመነ ብሉይ በሕግ ኦሪት፣ ተራምዶ መዳረሻውን ሕገ ወንጌል ያደረገ ጥንታዊ ክርስቶሳዊና ሐዋርያዊ ትምህርተ ሃይማኖት፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን፣ በያሬዳዊ ጣዕመ ዜማ የታጀበ ሥርዐተ አምልኮ፣ በጽሑፍና በትውልድ ቅብብሎሽ የተወረሰ የረጅም ጊዜ ትውፊት ባህልና ታሪክ

  • በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የበለጸገ፣ እግዚአብሔርን የሚወድና የሚፈራ ለእግዚአብሔር የሚታዘዝና ምክረ ካህን የሚቀበል ከስልሳ ሚልዮን በላይ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ

  • ለምጣኔ ሃብት ዕድገት እጅግ የምትጠቅም በውብ ሥነ ተፈጥሮና በሥነ ጽሑፍ፣ በሥነ ጥበብና በኪነ ጥበብ፣ በታሪክና በቅርስ ሃብት የበለጸገች እንዲሁም በሃይማኖት፣ በነጻነትና በአንድነት የደመቀች ሃገር

  • የእግዚአብሔርን ቃል ከሃገር ውስጥ ባሻገር ለመላው ዓለም ማዳረስ የሚችሉ ከግማሽ ሚልዮን ያላነሱ ሊቃውንት፣ ቀሳውስት፣ ዲያቆናት፣ ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ከሁለት ሺሕ ያላነሱ ገዳማት

  • መላውን ዓለም እያዳረሰና እየሰፋ የሚገኝ ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ የተዋቀረ ጠንካራ መዋቅር ያላት መሆኗ

ያግኙን

+251 111 55 0098 P.O.Box 1283 A.A. 5 KILLO, ADDIS ABABA, ETHIOPIA በፌስቡክ ያግኙን የዩትዩብ ቻነል