ልማት በቤተ ክርስቲያን

ልዮ ዕትም መጽሔት

ይህ ”ልማት በቤተክርስቲያን“ የተሰኘ ልዮ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።

ዜናዎች እና ወቅታዊ ክንውኖች

በቡፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንየልዑካን ቡድን ድሬዳዋ አየር ማረፊያ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።

ታኅሣሥ ፲፯ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም

የሸገር ማረሚያ ቤት ታራሚዎች እውቀትና ጉልበታቸውን በማስተባበር ቤተክርስቲያን በማነጽ ላይ ናቸው።

ታኅሣሥ ፲፬ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም

የአባታችን የጻድቁ አቡነ ሳሙኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በእዣ ወረዳ ቤተክህነት በገጨ ምዕራፈ ቅዱሳን ቅዱስ አቡነ ሳሙኤል ወቅዱስ ዕሩፋኤል ገዳም በድምቀት ተከብሮ ዋለ።

ታኅሣሥ 13 ቀን 2017 ዓ.ም

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሽገር ከተማ ሀገረ ስብከት በቡራዩ ገፈርሳ ጉዴ መልካ ኖኖ ክፍላተ ከተማ ስር ያሉት የቤተክርስቲያን አገልጋዮች የ2017 ዓ.ም የጥምቀት በዓል አከባበርን አስመልክቶ ወይይት አደረጉ።

ታኅሣሥ 13 ቀን 2017 ዓ.ም

ለቤተክርስቲያኗ መሪ እቅድ ስኬት አገልጋይ ካህናትና ምእመናን የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተጠቆመ።

ታኅሣሥ 13 ቀን 2017 ዓ.ም

ሐዋርያዊ ጉዞ በአራቱ ወለጋ

ታኅሣሥ 13 ቀን 2017 ዓ.ም

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የምዕራብ ጎንደር ሀገረ ስብከት 6ኛ  ዓመት አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ተካሄደ።

ሕዳር 19 ቀን 2017ዓ.ም

የመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ዐመታዊ መታሰቢያ በዓል በመላ ኢትዮጵያ በሌዩ ልዩ ሥፍሬዎች ላይ በድምቀት  ተከብሮ ዋለ።

ሕዳር 12 ቀን 2017ዓ.ም.

የቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት ጥገና  መዘግየት በቅርሱ ህልውና ላይ ከፍተኛ ስጋትን አስከትሏል ተባለ።

ጥቅምት 28 ቀን 2017 ዓ.ም

በሲዳማ ሀገረ ስብከት በሀዋሳ ከተማ በደብረ ምጥማቅ መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን የመድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ የጥንተ ስቅለቱ መታሰቢያና የጻድቁ አባታችን የመባዓጽዮን በዓል በታላቅ ድምቀት ተከበረ።

ጥቅምት 27 ቀን 2017 ዓ.ም

በፌስቡክ ያግኙን

የኅትመትና ሚዲያ ዋና ክፍል

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ

የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ

የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ልማት በቤተ ክርስቲያን

ይህ ልዩ ዕትም መጽሔት ጽርሐ ምኒሊክ ወይም በተለምዶ መሐሙድ ሕንጻ በመባል የሚታወቀው ሕንጻ ፈርሶና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ ወጪ ተገንብቶ ለምርቃት መብቃቱን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተዘጋጀ።

ስለ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን

ርእይ

ሁለንተናዊ ስብእናው የተጠበቀ፣ በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የደመቀ፣ በእግዚአብሔር ቃል የተቃኘ መንፈሳዊና ሥጋዊ ጣዕመ ሕይወትን የተላበሰ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዝግጁ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ በሀገር አቀፍም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ በቀጣይነት በዝቶ ማየት

ተልእኮ

  • የእግዚአብሔርን ቃል ለሰው ልጆች ሁሉ ማስተማርና ማዳረስ

  • ሰውን በሁለንተናዊ ሰብእናው ማገልገልና ማዳን

  • ሰውን ሁሉ በነገረ መለኮትና በነገረ ጥበብ ትምህርት በማልማት በመንፈሳዊም ሆነ በሥጋዊ ሕይወቱ የተሻለ ኑሮ እንዲኖረው ማድረግ

  • ጥራትና ብቃት፣ ፍትሐዊነትና እኩል ተደራሽነት ያለው መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት ለሰው ሁሉ ማበርከት

  • የተለያዩ የልማት መርሀ ግብሮችን በመንደፍ ቤተ ክርስቲያንን በኢኮኖሚ ማበልጸግ

  • በቴክኖሎጂ ስልት የሚመራና አዋጭነቱ አስተማማኝ የሆነ የጠቅላላ ሀብት አስተዳደርና አጠቃቀም እንዲረጋገጥ ማድረግ

  • የሰው ልጆች ሁሉ እኩልነት፣ ሰላምና ፍትሕ፣ ፍቅርና ስምምነት እንዲጠበቅ ያላሰለሰ ጥረት ማድረግ

  • የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አሰራር ግልጽ፣ ለሁሉም ተደራሽና ችግር ፈቺ እንዲሆን ማድረግ

ዕሴቶች

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅሊናን የሚረታ፣ አእምሮን የሚመሥጥ፣ ከጥንተ ፍጥረት ተነሥቶ በዘመነ አበው በሕገ ልቡና፣ በዘመነ ብሉይ በሕግ ኦሪት፣ ተራምዶ መዳረሻውን ሕገ ወንጌል ያደረገ ጥንታዊ ክርስቶሳዊና ሐዋርያዊ ትምህርተ ሃይማኖት፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን፣ በያሬዳዊ ጣዕመ ዜማ የታጀበ ሥርዐተ አምልኮ፣ በጽሑፍና በትውልድ ቅብብሎሽ የተወረሰ የረጅም ጊዜ ትውፊት ባህልና ታሪክ

  • በሃይማኖትና በሥነ ምግባር የበለጸገ፣ እግዚአብሔርን የሚወድና የሚፈራ ለእግዚአብሔር የሚታዘዝና ምክረ ካህን የሚቀበል ከስልሳ ሚልዮን በላይ የሆነ ኦርቶዶክሳዊ የክርስቲያን ማኅበረሰብ

  • ለምጣኔ ሃብት ዕድገት እጅግ የምትጠቅም በውብ ሥነ ተፈጥሮና በሥነ ጽሑፍ፣ በሥነ ጥበብና በኪነ ጥበብ፣ በታሪክና በቅርስ ሃብት የበለጸገች እንዲሁም በሃይማኖት፣ በነጻነትና በአንድነት የደመቀች ሃገር

  • የእግዚአብሔርን ቃል ከሃገር ውስጥ ባሻገር ለመላው ዓለም ማዳረስ የሚችሉ ከግማሽ ሚልዮን ያላነሱ ሊቃውንት፣ ቀሳውስት፣ ዲያቆናት፣ ሰባክያነ ወንጌል እንዲሁም ከሁለት ሺሕ ያላነሱ ገዳማት

  • መላውን ዓለም እያዳረሰና እየሰፋ የሚገኝ ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ የተዋቀረ ጠንካራ መዋቅር ያላት መሆኗ

ያግኙን

+251 111 55 0098 P.O.Box 1283 A.A. 5 KILLO, ADDIS ABABA, ETHIOPIA በፌስቡክ ያግኙን የዩትዩብ ቻነል የቴሌግራም ቻነል