የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር በጽርሐ ተዋሕዶ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተካሔደ ።

January 9, 2025

ጥር 1 ቀን 2017ዓ.ም. ( አዲስ አበባ)
+ + +
በመርሐ-ግብሩ በርካታ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ክቡራን ምክትል ሥራ አስኪያጆች፣ ክቡራን የየመምሪያ ኀላፊዎች ክቡር የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ ክቡራን የድርጅቶች ሥራ አስኪያጆችና የመንፈሳዊ ኮሌጆች ዲኖች የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ሠራተኞች ክቡራን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሠራተኞች ፣ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ ክቡራን የአባት አርበኞች አባላት፣ ክቡራን የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፣ በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የጋሞ ብሔረሰብ ዘማርያንና ክቡራን ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

መርሐ -ግብሩ በጸሎተ ወንጌል የተከፈተ ሲሆን የየካ ደብረ ሳህል ቅዱስ ሚካኤል ካህናትና ዲያቆናት ጸሎተ ወንጌል አድርሰዋል። ከጸሎተ ወንጌል በመቀጠል የአንጋፋው የቅድስት ሥላሴ ዩንቨርሲቲ ደቀመዛሙርት በጎል ሰከበ በአጽርቅት ተጠብለለ (በበረት ተኛ በጨርቅ ተጠቀለለ) የሚለው ያሬዳዊ ዜማ አቅርበዋል። በመቀጠልም የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት የአድባራትና የገዳማት አስተዳዳሪዎች ተወካዮች የእንኳን አደረሰዎ መልእክት አስተላልፈዋል ። በመልእክታቸው እጅም ሳይነካው ድንጋይ ከተራራው ተፈንቅሎ ከብረትና ከሸክላ የሆነውን የምስሉን እግሮች ሲመታና ሲፈጭ አየህ።”— ዳንኤል 2፥34 የሚል የመጽሐፍ ቃል በማንሳት የእንኳን አደረሰዎ መልእክታቸውን የጀመሩ ሲሆን ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ በዐበይትና በንዑሳን በዓላት የሰጡትን መልእክትና ያደረጉትን ሐዋርያዊ ሥራዎች በዝርዝር አቅርበዋል።

ነገረ ልደቱን ስናከብር በመንፈሳዊ ሥራዎች ሊሆን እንደሚገባም አውስተዋል ። የአዲስአበባ ሀገረ ሰብከት የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች የቅዱስነታቸው መመሪያ በመቀበል የተጣለባቸውን አደራ እየተወጡ እንደሆነ በመግለጽ እና ወደፊትም የቅዱስነታቸውም መመሪያ ለመተግበር ዝግጁ መሆናቸው በማሳሰብ መልእክታቸውን አጠናቀዋል ። ከዚህ በመቀጠል በሰንበት ትምርህት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የማዕከላዊውያን የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት “እንዘ አምላክ ውእቱ እምሰማያት ወረደ ከመ ይቤዙ ዓለመ” አምላክ ሆኖ ሳለ ዓለም ይቤዥ ዘንድ ከሰማያት ወረደ የተሰኘውን ያሬዳዊ ዜማ አቅረበዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የጋሞ ብሔረሰብ ዘማርያን በአማርኛና በጋሞኛ ዝማሬ አቅርበዋል።

በመቀጠልም የደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ፣ የደብረ ጽጌ ቅድስት ድንግል ማርያም ገዳም ፣ የእቲሳ ተክለሃይማኖት ገዳም ፣ የምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም ፣የመናገሻ አምባ መድኃኔዓለም ገዳም እና የዐባይ ባንክ አክስዮን ማኅበር እንኳን አደረሰዎ በማለት ጸበል ጸዲቅ በቅዱስነታቸው አስባርከዋል። መርሐግብሩ ሊቃውንቱ በቅኔ እንኳን አደረሰዎ በሚሉበት የቀጠለ ሲሆን ከማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም የመጻሕፍት እና የቅኔ መምህር የሆኑት ሊቅ ጀምሮ ሌሎች ሊቃውንትም ቅኔ አቅርበዋል።

የመርሐ-ግብሩ መገባደጃ ላይ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራአስኪያጅ የባሕርዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስን በመወከል ክቡር ንቡረ ዕድ ኤልያስ አብርሃ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በመንፈሳዊ ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ቤትን የእንኳን አደረሰዎ መልእክት አስተላልፈዋል። የሰው ልጅ የክርስቶስን መምጣት እንዲጠባበቅ ያደረገው አንዱና ዋነኘው ምክንያት እጦት ነው። የሰው ልጅ በሠራው በደል ምክንያት ልጅነትን አጥቶ ስለነበረ ሐዲስ ልደት ማግኘት አስፈልጎታል። ለዚህም ምላሽ እንዲሆን በእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ቤዛነት ዳግም ልጅነትን አግኝቷል። የሰው ልጅ ደግም የወራሽነትን መብትን አግኝቷል። በልደተ ክርስቶስ ቀን ደስታና ሐዘን ታይተዋል። ደስታው የመላእክት ዝማሬ ሲሆን ሐዘኑ ደግሞ በሄሮድስ እኩይ ሐሳብ ምክንያት ብዙ ሕፃናች መሰዋታቸው ነው። ከዚህ የምናየው ክፉና በጎ በተሠሳሳይ ጊዜ ሊከሰቱ እንደሚችሉ ነው። ይህ ሁኔታ በዘመናችንም በቤተክርስቲያናችን ይገጥማታል ። ነገር ግን በቅዱስነትዎ በሳል የአመራር ጥበብ የሚመጡትን ተግዳሮቶች እንደ አስተማሪ እንዲሁም የሚመጡ መልካም ነገሮችን እንደ ገጸ በረከት በመጠቀም ስለሚሠሩ ሁሌም መልካም እንደሚሆን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ያምናል። በተለይም በወጣቱ ላይ ቢሠራና መሪ እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ የምናደርገው ጥረት ቤተክርስቲያንን የሚያሻግር መሆኑን በመግለጽ የእንኳን አደረሰዎ መልእክታቸውን አጠናቀዋል።

ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የእንኳን አደረሰዎ መልዕክት በመቀጠል በበብፁዕ አቡነ ማርቆስ ጋባዥነት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ለታዳሚዎች ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጥትዋል።

ቅዱስነታቸው በሰጡት አባታዊ መመሪያ ታዳሚዎችን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት ጀምረው በዓለ ልደትን ያከበርንበትን ሰላማዊ አገልግሎት በማድነቅ የክርስቶስ መወለድና ወደዚህ ምድር መምጣትን ዋነኛ ዓላማን አብራርተዋል። በሁለት ሰዎች ስህተት ምክንያት የዘመናት ውድቀት ተከስቷል። ዘመኑም ዓመተ ፍዳ ተብሏል ። ነገርግን ከክርስቶስ ልደት በኋላ ዘመን ተቀይሮ ዓመተ ምህረት ተብሏል። ጥንትም ቢሆን ሰዎችን ሲፈጥር ባለ አእምሮ አድርጎ ነው ። ነገር ግን ካደረጉት የጥንቃቄ ጉድለት የተነሳ ለውድቀት ተዳርገዋል። ባለ አእምሮ ሆነን ሳለን አልሠራንበትም እንስሳት ባለአእምሮ የአይደሉም ነገር ግን ተንሸራተው ካልሆነ በቀር እያዩ ገደል አይገቡም እኛ ግን ባለ አእምሮዎች ሆነን ተፈጥረን እያወቅን ወደ ገደል እንሮጣለን።

እግዚአብሔር አእምሮውን ይስጠን በማለት ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጥተው የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ አርሲ-አቦምሳ ወረዳ ተገኝቶ ምዕመናንን አጽናና ጊዜያዊ ርዳታም አበረከተ።
  • “በአርሲ የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን እንሠራለን” የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች
  • ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በሀገረ ስብከቱ ለካህናት የሚሰጠውን ሥልጠና በጸሎትና በቡራኬ አስጀመሩ።
  • ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ተገኝተው የተጎዱ ወገኖችን የሚያጽናኑ በፁዐን አባቶችን መደበ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን የልዑካን ቡድን ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሰላም ሚኒስቴርና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያየ።

Archives

  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: መልእክተ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ Link to: መልእክተ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ መልእክተ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ Link to: ለአንድ ዓመት ያህል የሠለጠኑ ፳፪ ካህናት ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ዶ/ር በተገኙበት ተመረቁ። Link to: ለአንድ ዓመት ያህል የሠለጠኑ ፳፪ ካህናት ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ዶ/ር በተገኙበት ተመረቁ። ለአንድ ዓመት ያህል የሠለጠኑ ፳፪ ካህናት ብፁዕ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top