የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ

January 19, 2025

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ፣የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣
ክቡር——————————————————————–
ክብርት —————————————————————-
ክቡራን የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣
ክቡራን አምባሳደሮችና የኮር ዲፕሎማቶች፣
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የየመምሪያው ኃላፊዎች፣
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣
የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች፣

በአጠቃላይ በቅርብና በሩቅ ሆናችሁ የ2017 ዓ.ም በዓለ ጥምቀት እያከበራችሁ የምትገኙ ሕዝበ ክርስቲያኖች በሙሉ፣
በመጠመቁ የክዋኔ ልጅነቱን አስመስክሮ የጸጋ ልጆች እንድንሆን ያበቃንን ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓመት ምሕረት የጥምቀተ ክርስቶስ በዓል አደረሰን አደረሳችሁ፡፡

ወመጽአ ቃለ እግዚአብሔር ኀበ ዮሓንስ ወልደ ዘካርያስ፤የእግዚአብሔር ቃል ወደ ዘካርያስ ልጅ ወደ ዮሓንስ መጣ (ሉቃ ፩÷፪፤)
የመሲሑ መንገድ ጠራጊ ሆኖ እንዲያገለግል በእግዚአብሔር ዘንድ ከዘመናት በፊት የተመረጠው ዮሓንስ ወልደ ዘካርያስ ከእናቱ ማሕፀን ጀምሮ በመንፈስ ቅዱስ የተሞላ ነበር፤ ቅዱስ ዮሓንስ በዮርዳኖስ በረሃ በብሕትውና ሕይወት በነበረበት ወቅት የእግዚአብሔር ቃል ወደ እርሱ መጣ፤ ወደ እርሱ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ የሚል ነበር፡-
‹‹የጌታን መንገድ አዘጋጁ፤ ጥርጊያውንም አቅኑ፣ዓዘቅቱ ሁሉ ይሙላ፤ ተራራውና ኮረብታውም ሁሉ ዝቅ ይበል፤ ጠማማውም የቀና መንገድ ይሁን ፤ሸካራውም መንገድ ይስተካከል፤ ሥጋም የለበሰ ሁሉ የእግዚአብሔርን ማዳን ይይ››፤

መጥምቁ ዮሓንስ ይህንን የድኅነት መልእክት ከእግዚአብሔር የመጣለት በገዳመ ዮርዳኖስ ባሉ ከተሞች እያስተማረና ሕዝቡን ለንስሐ እያዘጋጀ በነበረበት ጊዜ ነው፤ የትምህርቱ ዋና ይዘትም የጌታ መንገድ የሰው አእምሮ መሆኑን በማስገንዘብ ጌታ በዚህ መንገድ እንዲጓዝበትና እንዲመላለስበት በደንብ ይዘጋጅ የሚል ነው፤

የዝግጅቱም ሁናቴ በዝርዝር ሲገለጽ ተስፋ በመቁረጥ እንደ ዓዘቅት የጐደጐደውና የጨቀየው አእምሮ በተስፋ ድኂን ቀና ይበል፤
በሥልጣን፣ በዕውቀት፣በሀብትና በወገን ከሁሉ የላቀ እንደሆነ የሚያስብም እንደማንኛውም ሰው መሆኑን ተረድቶ እኩልነትን ተቀብሎና ኣክብሮ ይኑር፤ በክፋትና በምቀኝነት፣ በተንኮልና በሴራ አተርፋለሁ የሚል ጠማማ አእምሮም ወደ ቅን አስተሳሰብ ይመለስ፤ በቂም፣ በበቀልና በጥላቻ ተዘፍቆ የሚኖር ልብም በሰላም በፍቅርና በስምምነት ወደሚገኝ የተስተካከለ ጣዕመ ሕይወት ይግባ ማለት እንደ ሆነ እናስተውላለን፤

ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣
የተከበራችሁ የበዓሉ ተሳታፊዎች!

እግዚአብሔር ምድርና ሰማየ ሰማያት የማይችሉት ምሉእ፤ረቂቅና ስፉሕ ነው፤

ይሁን እንጂ በቅዱሳን ሰዎች አእምሮ ውስጥ ማደርና ማረፍ በእጅጉ የሚሻ አምላክ እንደሆነ ደጋግሞ ገልጾአል፤መመላለሻውም በሰው ኅሊና፣ በሰው ልቡና እና አእምሮ ውስጥ እንደሆነ አልሸሸገም፤ያም በመሆኑ መንገዱና ጥርጊያው የሆነ የእኛ አእምሮ ቀጥ ያለና ይማይጐረብጥ እንዲሆንለት ያዘናል፤

መጥምቁ ዮሓንስም ይህ ዓይነቱ ዝግጅት በሰው አእምሮ ውስጥ እንዲኖር ለመቀስቀስ ተልኮአል፤
ዝግጅቱ የጠቅላላ ስራው መቋጫ አልነበረም፤ የዝግጅቱ ዋና መቋጫ ሰው ሁሉ እንደ ስምዖን የእግዚአብሔርን ማዳን በዓይኑ አይቶ በአእምሮው አስልቶ በልቡ ኣምኖ የድኅነቱ ባለቤት መሆን ሲችል ነው፤ የእግዚአብሔር ፈቃድና ፍላጎትም ይኸው ነው፤ ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የኛን ሰውነት በመዋሐድ አምላክና ሰው ሆኖ በዚህ ዓለም እንዲገለጥ ያስፈለገበት ዓቢይ ምክንያትም ይኸው ነው፤ ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ በዛሬው ዕለት በፈለገ ዮርዳኖስ የፈጸመው ምስጢረ ጥምቀት ሰው የሚያድንበት ዕድል ምን እንደሆነ ለማስረዳት ነው፤

ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣
የተከበራችሁ የበዓሉ ተሳታፊዎች!

ሰው በራሱ ዘላቂ ሕይወት የለውም፤ የሕይወት ምንጭ እግዚአብሔር ብቻ ነው፤ ሰው ዘላቂ ሕይወትን ማግኘት የሚችለው የሕይወት ምንጭ ከሆነው ከእግዚአብሔር ጋር ልዩ ግንኙነት ሲኖረውና በግንኙነቱ አማካኝነት ዘላዓለማዊ ሕይወት ከእግዚአብሔር ሲቀዳጅ ነው፤ ይህንንም ልዩ ግንኙነት የሚያገኘው ከእግዚአብሔር ሲወለድ ነው፤ ለመወለድ ደግሞ በእግዚአብሔር የማዳን ስራ ማመንና መጠመቅ ሲቻል ነው፤ ሰው ሲጠመቅ የእግዚአብሔር ልጅ ይሆናል፤
እግዚአብሔርም በልጁ አእምሮ ውስጥ በሃይማኖት በአምልኮና በምስጋና ይመላለሳል፤ ያድራል፤ ያርፋልም፤ ሥጋ የለበሰ ሁሉ የእግዚአብሔርን ማዳን ይይ የተባለውም ይህንን ልጅነት ነው፤

በዚህ ልጅነት ምክንያት ሰው የዘላለም ሕይወት ባለቤት ሆኖ ይኖራል፤ ጥምቀት ለሰው ልጆች የሚያስገኝልን ጸጋ ይኸው ነው፤

ታዲያ የእግዚአብሔር የዝግጅት ጥሪ ዘላዓለማዊ ሕይወትን ለማደል ሆኖ ሳለ የተጠበቀው ዝግጅት ግን ከሰው እየታየ ኣይደለም፤

ዛሬም እኛ ሰዎች አእምሮችን ጐድጓዳ ዓዘቅት ሆኖ በመቀጠሉ ለጉዞ አልተመቸውም፤
ዛሬም ልባችን ከተራራና ኮረብታ ባልተናነሰ ሁናቴ ትዕቢት እንደተሞላ ነው፤ ከቅንነት ይልቅ ጠማማነት፤ ከእውነት ይልቅ ማሴር የየዕለት ተግባር አድርገነዋል፤

በዚህም እግዚአብሔር ከኛ እንዲርቅ አድርገናል እሱም በኣጸፋው ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጥቶናል፤ ዓለማችን በአሁኑ ጊዜ ያላት ምስል ይኸው ነው፤

ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣
የተከበራችሁ የበዓሉ ተሳታፊዎች!

ዓለማችን አሁን ያለችበት ምስል ለሰው ልጅ ሁሉ በጣም አሳሳቢና አስፈሪ ነው፤ ለእግዚአብሔር አልታዘዝም ብሎ በነውረ ኃጢአት መጋለብና ለጦርነትና ለዕልቂት የሚሆን መሳሪያ በማምረት መሽቀዳደም የሚበጅ አይደለም፤

ከዚህ ይልቅ ዓለማችን አሁንም ቆም ብላ ብታስብና ሕይወት ወደ ሆነው እግዚአብሔር እንድትመለስ በእግዚአብሔር ስም እንመክራለን ፤

በሰው ልጆች የሚታይ መሠረታዊ ችግር ከእግዚአብሔር መለየትና ለእሱ ያለመታዘዝ እንጂ የሀብት ዕጥረት አይደለም፤

ምድሪቱ ኁልቈ መሥፈርት የሌለው ሀብት በውስጥም በውጭም አጭቃ ይዛለች፤ እሱን በፍቅርና በስምምነት ብናለማው ከበቂ በላይ ነው፤

እሱም ቀርቶ ያለውን ለጦርነትና ለዕልቂት ከምናውለው ለልማት ብናውለው ችግርና እጦት ከምድራችን በጠፋ ነበር፤

አሁንም ራሳችንን በራሳችን ከማጥፋት ተቆጥበን የምድራችንን የአየር ንብረትና የተፈጥሮ ሥነ ምኅዳር በመጠበቅ ግጭትንና ጦርነትን በማስቆም ለተመደበልን ሰላማዊ ሕይወት ልንተጋ ይገባል፣

በመጨረሻም

በዓለ ጥምቀቱ ከእግዚአብሔር የምንወለድበትን ዕድል የከፈተ ነው፤ በዚህም ዕድል የእግዚአብሔር ልጆች ለመሆን በቅተናል፤

ስለሆነም የእግዚአብሔር ልጆች ለመሆናችን ልዩ ምልክታችን የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የፍትሕና የእኩልነት ሰዎች ሆነን እንድንገኝ ነውና በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ያላችሁ ልጆቻችን ሁሉ በሃይማኖት ጸንታችሁ ለሰላምና ለአንድነት ከምንጊዜውም በላይ የበኩላችሁን ጥረት ታደርጉ ዘንድ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡

በዓለ ጥምቀቱን የሰላምና የበረከት ያድርግልን
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጰሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ
ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣

ጥር ፲፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ አርሲ-አቦምሳ ወረዳ ተገኝቶ ምዕመናንን አጽናና ጊዜያዊ ርዳታም አበረከተ።
  • “በአርሲ የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን እንሠራለን” የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች
  • ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በሀገረ ስብከቱ ለካህናት የሚሰጠውን ሥልጠና በጸሎትና በቡራኬ አስጀመሩ።
  • ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ተገኝተው የተጎዱ ወገኖችን የሚያጽናኑ በፁዐን አባቶችን መደበ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን የልዑካን ቡድን ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሰላም ሚኒስቴርና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያየ።

Archives

  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የእድሳት ሥራ ተጠናቆ በቅዱስ ፓትርያርኩ እየተመረቀ ነው። Link to: የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የእድሳት ሥራ ተጠናቆ በቅዱስ ፓትርያርኩ እየተመረቀ ነው። የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የእድሳት... Link to: የጥምቀት በዓል ብፁዕ አቡነ አብርሃም በተገኙበት በባሕር ዳር በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ። Link to: የጥምቀት በዓል ብፁዕ አቡነ አብርሃም በተገኙበት በባሕር ዳር በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ዋለ። የጥምቀት በዓል ብፁዕ አቡነ አብርሃም በተገኙበት...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top