የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት እንዲሁም በመላው ዓለም የምትገኙ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምዕመናን ወምዕመናት እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ በሰላም አደረሳችሁ አሸጋገራችሁ

September 10, 2024

“ወትባርክ አክሊለ ዓመተ ምሕረትከ ወይጸግቡ ጠላተ ገዳም –  በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፥ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል” መዝ ፡ ፷፬ ( ፷፭ ) ፥ ፲፩

ከላይ የተገለጸው ኃይለ ቃል የአምላካችንን ድንቅ መጋቢነት የሚገልጽ ሲሆን፤ እግዚአብሔር አምላካችን ዓመታትን በቸርነቱ እየለወጠ፤ የበረከት እጁን ሳያጥፍ እየመገበ፤ የሰዎችን ማንነት ሳይለይ ለክፉም ለደጉም፤ ለኃጥኡም ለጻድቁም፣ ለድሀውም ለሀብታሙም፣ ለአሕዛብም ለሕዝብም የምሕረት ዝናቡን እያወረደ ፍጥረትን በሙሉ የሚያረካ አምላክ እርሱ ብቻ መሆኑን ያስረዳናል። እንዲሁም ሥነ-ፍጥረትን ብንመረምር የበጋና የክረምት መፈራረቅ፤ ተራሮች በዝናብ መርካታቸው፤ ከድርቀት (ከፀሐይ) ወራት በኋላ የሚመጡት የበረከት (የዝናብ) ጊዜያት እንዴት ባለ በሚያስደንቅ ሁኔታ የምድሪቱን ገጽታ እንደሚቀይር እንገነዘባለን።

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን

አሮጌው ዘመን አልፎ አዲሱ ዘመን ሲተካ በምን ዓይነት መንፈስ ነው የምንቀበለው ለሚለው ጥያቄ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ምላሽ ይሰጠናል። «የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት፤ በመዳራት እና በሥጋ ምኞት፣ በስካርም፣ በዘፈንም፣ ያለልክም በመጠጣት፣ ነውርም ባለበት፣ በጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና» በማለት ያስተምረናል። (1ጴጥ.፬፥፫) ዘመናትን በቸርነቱ የሚያሳልፈው እግዚአብሔር ነው፡፡ በተሰጠን የአንድ ቀን ዕድሜ ኖሬበታለሁ? ብለን ራሳችንን ልንመረምር ይገባል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ በኃጢአት የኖርበትን ዘመን በሕይወት እንዳልኖርበት ነግሮናል፡፡ ለምን ቢባል በደሙ የከበርን ክርስቲያኖች አምላካችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መስለን ባለመገኘታችን ነው፡፡

በክርስቶስ ክርስቲያን ተሰኝተን በጥምቀት ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ተወልደን የማይጠፋውን ልጅነት ካገኘን በኋላ መጠመቃችንን የክርስትና መጨረሻ አድርገን በመውሰድ በስም ብቻ ክርስቲያኖች በመባል በክፋት ጸንተን እንገኛለን፡፡ ሥራ የሌለው እምነት ፣ፍሬ የሌላት በለስ ሆነን ከመገኘት ክርስትናን ኖረንበት ልናልፍ ይገባል፡፡

እግዚአብሔር በቸርነቱ ዘመንን ያቀዳጀን በመንፈሳዊ ሕይወት ታድሰን ተለውጠን አዲስ የተሻለ መንፈሳዊ ሰው እንድንሆን ነው። አዲስ ሰው መሆን ማለት ያለፈ ዘመንን ክፉ ግብር/ሥራ/ መተው፣ ደግሞም ኃጢአት ላለመስራት መታቀብና ራስን መግዛት ነው።እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ለመጨረሸዋ የፍርድ ቀን መልካምን ቃል የሚያሰማንን ተግባር ለማከናወን ለመልካም ሥራ መነሳሳት፣ የመንፈስ ፍሬያትን ማፍራት ያስፈልጋል። «የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም፣ ትዕግሥት፣ ቸርነት፣ በጎነት፣ የውሃት፣ ራስን መግዛት ነው።» ገላ፭፥ ፳፪

“እነሆ የመዳን ቀን አሁን ነው።” (፪ኛ ቆሮ ፮፥፪) ባሳለፍነው ዓመት በሀገራችን ብሎም በዓለማችን እጅግ በጣም ብዙ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ክስተቶችን አሳልፈናል። ለአብነትም ያኽል በሰሜኑ እንዲሁም በተለየዩ በሀገራችን ክፍሎች እጅግ በጣም ብዙ ንጹሐን ሕይወታቸውን አጥተዋል ፣ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል ፣ ብዙ ሕጻናት ወላጅ አልባ ሆነዋል። ምንም በማያውቁት እጅግ በጣም ብዙ ንጹሐን የጦርነት ሰለባ ሲሆኑ ተመልክተን አዝነናል። እንዲሁም በተፈጥሯዊ ክስተት ደግሞ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች በተለይም በሰሜኑ እና በደቡቡ የሀገራችን ክፍል በመሬት መንሸራተት ምክንያት ብዙ ወገኖቻችን ለሞት ፣ ለከፍተኛ የአካል ጉዳት እንዲሁም ቀላል ለማይባል ለኢኮኖሚያዊ ፣ ለማኅበራዊ እና ለስነ-ልቦናዊ ጉዳት እንደተዳረጉ እንገነዘባለን።

በዚህ ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ቀውስ ምክያንት ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን እግዚአብሔር አምላካችን ሐገረ ሕይወትን መንግስተ ሰማያትን እንዲያወርስልን ፣ ከቤት ንብረታችሁ ተፈናቅላችሁ ላላችሁ አምላካችን በሰላም ወደመንደራችሁ እንዲመልሳችሁ ፣ ቤተሰቦቻችሁን በሞት አጥታችሁ ላላችሁ ልጆቻችን መጽናናቱን እንዲልክላችኹ ሰላም ላጡ ሁሉ ሰላማቸውን እንዲመልስላቸው የዘወትር ጸሎታችን ነው።

በዘመነ ማቴዎስ እጅግ በጣም ብዙ የበደሉንን ይቅር ብለን ፣ የበደልናቸውን ክሰን ፣ ለሰው ሁሉ ፍቅርን ሰጥተን ፣ ፍቅርን በመቀበል ፣ የፍቅር አምላክ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልጆች መሆናችንን በግልጥ የምናሳይበት የፍቅር ፣ የሰላም ፣ የደስታ ፣ የጤና ፣ የበረከትና የመተሳሰብ ፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ ለጥፋት ፣ ሕዝቡ ለስደት የማይዳረግበት ዘመን ይሆንልን ዘንድ እንዲሁም ከኃጢአታችን በንስሐ ውኃ የምንታጠብበት፣ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለእኛ በቀራንዮ የቆረሰልንን ቅዱስ ሥጋውን የምንበላበት፣ ያፈሰሰልንን ክቡር ደሙን የምንጠጣበት ዘመን እንዲሆንልን እግዚአብሔር አምላካችንን በጸሎት ልንለምን ይገባል።

 

“እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
አባ ገሪማ
የጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/abune-gerima-cover.jpg 445 400 tc https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg tc2024-09-10 19:16:442024-09-10 19:17:02በጌዴኦ ኮሬና ቡርጂ ሀገረ ስብከት እንዲሁም በመላው ዓለም የምትገኙ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምዕመናን ወምዕመናት እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ በሰላም አደረሳችሁ አሸጋገራችሁ
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: “አስመ የአክለክሙ ዘኀለፈ መዋዕል ዘገበርክሙቦቱ ፈቃዶሙ ለአህዛብ”“የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና” /1ኛ ጴጥ. 4፥3/፡፡ Link to: “አስመ የአክለክሙ ዘኀለፈ መዋዕል ዘገበርክሙቦቱ ፈቃዶሙ ለአህዛብ”“የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና” /1ኛ ጴጥ. 4፥3/፡፡ “አስመ የአክለክሙ ዘኀለፈ መዋዕል ዘገበርክሙቦቱ... Link to: ብጹዕ አቡነ ዮሴፍ አዲሱን ዓመት አስመልክቶ ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው ያስተላለፉት አባታዊ መልእክት። Link to: ብጹዕ አቡነ ዮሴፍ አዲሱን ዓመት አስመልክቶ ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው ያስተላለፉት አባታዊ መልእክት። ብጹዕ አቡነ ዮሴፍ አዲሱን ዓመት አስመልክቶ ለመንፈስ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top