ከአዲስአበባ ሀገረ ስብከት አጣሪ ኮሚቴ የተሰጠ ማሳሰቢያ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በአዲስአበባ ሀገረ ስብከት የተከሰተውን የመልካም አስተዳደር ችግር አጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር የሚያቀርብ ኮሚቴ አቋቁሞ ወደ ሥራ እንዲገባ ማድረጉ ይታወቃል።
ይህንን ተከትሎ የተቋቋመው ኮሚቴ መረጃዎችን ለመሰብሰብ፣
ለማደራጀትና ለመተንተን ያስችለው ዘንድ ቀደም ሲል ባደረገው ጥሪ መሠረት መረጃዎችን ማሰባሰብ መጀመሩ ይታወቃል።
ይሁንና አንዳንድ መረጃ ያቀረቡ ሰዎች ከግንቦት 2017 ዓ.ም
እስከ ሐምሌ 2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ ያሉ መረጃዎችን መስጠት ሲገባቸው ከሁለት ዓመታት በፊት በሀገረ ስብከቱ በደል ደርሶብናል የሚሉ ጭምር ማስረጃዎቻቸውን እያደረሱን መሆኑን ተመልክተናል።
ስለሆነም አጣሪ ኮሚቴው ከግንቦት 2017 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 2018 ዓ.ም ድረስ በደል ደርሶብናል የሚሉ በርካታ ማረጃዎችን እየተቀበለ መሆኑን ከመግለጽ ጋር በቀሪዎቹ ሦስት ቀናት ብቻ ቀረ የምትሉትን ማስረጃ ለኮሚቴው እንድታደርሱ እያስታወቅን ከአርብ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በኋላ የተሰበሰቡትን መረጃዎች በመተንተን ወደ ጭብጥ በመቀየር የጥናቱ ግብዓት የማድረግ ሥራ ብቻ የሚያከናውን ስለሆነ ማስረጃዎችን የማይቀበል መሆኑን ከወዲሁ ይገልጻል።
አጣሪ ኮሚቴው
ነሐሴ19 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ