የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ዓመታዊ የሥልጠናና የውይይት መርሐ ግብሩን ጀመረ።

February 8, 2024

ጥር ፴ ቀን ፳፻፲ወ፮ ዓ/ም አዲስ አበባ።
+ + +

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ በየዓመቱ የሚያካሂደውንና ወዘቅታዊና ዘላቂ የቤተክርስቲያናችን ጉዳይ ላይ በየዓመቱ የሚያደርገውን የሁለት ቀናት የሥልጠናና የውይይት መርሐ ግብር ዛሬ ጥር ፴ ቀን ፳፻፲ወ፮ ዓ/ም ጀመረ።

“ለክርስቶስ ወንጌል እንደሚገባ ኑሩ” (ፊል.፩፥፳፯) የሚለውን የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት የጉባኤው መሪ ቃል ያደረገው መምሪያው ስብከተ ወንጌል የቤተክርስቲያናችን ዋና ተልእኮ ከመሆኑ አንጻር ከፍተኛ ትኵረት ተሰጥቶት ዘመኑን የዋጀ የስብከተ ወንጌል ተደራሽነትን ማረጋገጥ፣ የቅድስት ቤተክርስቲያንን መዋቅራዊ ትሥሥር ማጠናከርና የአገልጋዮችን አእምሮአዊና መንፈሳዊ ክሂሎት ላይ አበክሮ ለመሥራት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን የመምሪያው ኃላፊ መ/ሰ. ቆሞስ አባ ቃለጽድቅ ሙሉጌታ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

መርሐ ግብሩን በጸሎት የከፈቱትና አባታዊ መልእክታቸውን ያስተላለፉት የመምሪያው የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ “ከሁሉ በፊት የምንሰብከውን የወንጌል እውነት እንኑረው፤ ከዚያ በኋላ ሁሉም ይከናወንልናል፤ ችግር እየገጠመን ያለው የምንሰብከውን ባለመኖራችን ነው፤” ሲሉ መልእክታቸውን በማስተላለፍ ውይይቱ ተግባር ተኮር እንዲሆን አባታዊ መመሪያ ሰጥተዋል።

በዛሬው መርሐ-ግብር ላይ ዕቅበተ እምነትንና በአገልግሎት ላይ የሚፈጠሩ ተግዳሮቶችን እንዴት ማለፍ ይገባል በሚል ርእሰ ጉዳይ ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

የዕለቱን መርሐ-ግብር በጸሎት እንዲከፍቱና አባታዊ መልእክት እንዲያስተላልፉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት እቅድ ይዘው የነበረ ቢሆንም በወቅታዊ ጉዳይ የመርሐ-ግብር መደራረብ ምክንያት ሳይገኙ ቢቀሩም አባታዊ መልእክታቸውን በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በኩል አስተላልፈዋል። የብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አባታዊ መልእክትም በክቡር ምክትል ሥራ አስኪያጅ በኩል ተላልፏል።

በመርሐ-ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የኢትዮ ሱማሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ቶማስ የአዊና መተከል አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ሊቀ አእላፍ በላይ መኮንን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ምክትል ሥራ አስኪያጅ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የመምሪያና የድርጅት ኃላፊዎች፣ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የዋና ክፍል ኃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማ አብያተ ክህነት የስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊዎችና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አድባራትና የገዳማት የስብከተ ወንጌል ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የመርሐ-ግብሩ አስፈላጊ ወጪዎች በኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበርና በአሐዱ ባንክ አ.ማ. መሸፈኑ በመምሪያው ተገልጿል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ አርሲ-አቦምሳ ወረዳ ተገኝቶ ምዕመናንን አጽናና ጊዜያዊ ርዳታም አበረከተ።
  • “በአርሲ የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን እንሠራለን” የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች
  • ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በሀገረ ስብከቱ ለካህናት የሚሰጠውን ሥልጠና በጸሎትና በቡራኬ አስጀመሩ።
  • ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ተገኝተው የተጎዱ ወገኖችን የሚያጽናኑ በፁዐን አባቶችን መደበ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን የልዑካን ቡድን ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሰላም ሚኒስቴርና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያየ።

Archives

  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ አገር እንዳይገቡ ተከለከሉ። Link to: ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ አገር እንዳይገቡ ተከለከሉ። ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ አገር እንዳይገቡ ተከ... Link to: ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በትላንትናው እለት የብፁዕ አቡነ ፋኖኤል የዋሽንግተን ዲሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወላጅ እናት የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ተከኝተው አሸኛኘት አደረጉላቸው። Link to: ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በትላንትናው እለት የብፁዕ አቡነ ፋኖኤል የዋሽንግተን ዲሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወላጅ እናት የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ተከኝተው አሸኛኘት አደረጉላቸው። ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በትላንትናው እለት...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top