የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

በቡፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የሚመራ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንየልዑካን ቡድን ድሬዳዋ አየር ማረፊያ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።

December 27, 2024

ታኅሣሥ ፲፯ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም
******
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ

በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የሚመራ ፲ የልዑካን ቡድን ዓመታዊውን የቅዱስ ገብርኤል በዓል ለማክበር ፣በበዓሉ ላይ ለሚገኙ ምዕመናንን ትምህርተ ወንጌል፣ቃለ በምዕዳንና ቃለ ቡራኬ ለመስጠት ዛሬ ማለዳ ድሬዳዋ ገብተዋል።

የልዑካን ቡድኑም፦
1- ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የዳውሮ ኮንታ ከንባታ ሐላባና ጠምባሮ አህጉረ ስብከት ጳጳስ
2- ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የኢትዮ ሶማሌ ጅግጅጋ ሀገረ ስብከት ጳጳስ
3- ብፁዕ አቡነ ኤጲፋንዮስ የምሥራቅ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስ
4- ክቡር ንቡረእድ ኤልያስ አብርሃ የመ/ፓጠ/ቤ/ክ መንፈሳዊ ዘርፍ መ/ሥራ አስኪያጅ
5-መ/ሕ ቆሞስ አባ ኃይለገብርኤል ነጋሽ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት ኀላፊ
6- መ/ካ ዕንቈባሕርይ ተከስተ የመ/ፓጠ/ቤ/ክ የካህናት አስተዳደር መምሪያ ኀላፊ
7- መ/ር አካለወልድ ተሰማ (ደ/ር) የመ/ፓጠ/ቤ/ክ አስተዳደር መምሪያ ኀላፊ
8- ሊ/ስ እስክንድር ገ/ክርስቶስ የመ/ፓጠ/ቤ/ክ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኀላፊ
9-ሊቀ ነብያት ሙሴ ኀይሉ የቅዱስ ፓትርያርኩ ፕሮቶኮል ተጠሪእና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተጉዘዋል።

ቅዱስ ፓትርያርኩ እና የልዑካን ቡድኑ ድሬዳዋ አውሮፕላን
ማረፊያ ሲደርሱ በብፁዕ አቡነ በርተሎሚዎስ የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ጳጳስ፣በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ በአቶ ከድር ጁዋርና በካቢኔ አባለቱ፣ በሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች፣ በካህናትና በሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች የክብር አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በድሬዳዋ አውሮፕላን ማረፊያ በመገኘት ለቅዱስነታቸውና ለልዑካን ቡድኑ ደማቅ አቀባበል ያደረጉለት የድሬዳዋ ከንቲባ አቶ ከድር ጅዋር በክብር ዘብ፣በፖሊስ የማርሽ ቡድንና በፈረሰኛ የታጀበ ደማቅና የክብር አቀባበል በማድረግ እንኳን ደህና መጣችሁ፣
እንኳንም አደረሳችሁ ብለዋል።

በመቀጠልም በድሬዳዋ ርእሰ አድባራት ወገዳማት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የእንኳን ደህና መጡ መርሐ ግብር የተካሔደ ሲሆን ብፁዕ አቡነ በርተሎሜዎስ የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።በመልዕክታቸውም የድሬዳዋ ከንቲባ ከኮሪደር ልማቱ ጋር በተያያዘ አብያተክርስቲያናት እንዳይነኩ በማድረግና በልማቱ ሱቃቸው ለፈረሱባቸው አብያተክርስቲያናትም የካሳ ክፍያ በመፈጸም እያደረጉት ላለው ከፍተኛ አስተዋጽኦ አመስግነዋል።

የድሬዳዋ ከተማ ከንቲባ አቶ ከድር ጅዋር በበኩላቸው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ በእንግዳ አክባሪነቷ የምትታወቀውና ሁሉም ተቻችሎ የሚኖርባት ከተማችን የቅዱስ ገብርኤል በዓልን ለማክበር የመጡ እንግዶች ሁሉ ተደስተውና ከተማችንን እንደቤታቸው ቆጥረው እንዲቆዩ በማድረግ የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንድታደርጉ አደራ እላለሁ ብለዋል።

በመጨረሻም ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ለልዑካኑ ስለተደረገው አቀባበል አመስግነው የሁሉም ኢትዮጵያዊ ያን ከተማና የአንድነት ተምሳሌት በሆነችው ድሬዳዋ ከተማ አንድነትና ሰላማችሁን፣ፍቅራችሁን፣ ጠብቃችሁና በጸሎት ጸንታችሁ ለመኖር ያብቃችሁ የቅዱስ ገብርኤልን በዓል ለማክበርና ከበረከቱ ለመሳተፍ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል የመጣችሁ ልጆቻችን እግዚአብሔር አምላክ በዓሉን በሰላም አሳልፋችሁ ወደየመጣችሁበት በሰላም ይመልሳችሁ ካሉ በኋላ የድሬዳዋ ከተማ ከንቲባ አቶ ከድር ጅዋር የደግነትና የአንድነት ተምሳሌት መሆናቸውን ሁሉም ስለሚያውቀው ብዙ መናገር አያስፈልገውም ብለዋል።

በሁሉም የሀገሪቱ ክፍል እየተካሔደ ያለው የኮሪደር ልማት ቤተክርስቲያንን እንዳይነካ ከመንግስት ኃላፊዎች ጋር በመነጋገራችን እስከ አሁን የተነካ ቤተክርስቲያን የለም ያሉት ቅዱስነታቸው በተለይ ደግሞ የድሬዳዋ ከንቲባ የቤተክርስቲያን ድምጽ ሰምተው ወቅታዊና ፈጣን ምላሽ የሚሰጡ ሰለሆነ ምንም አይነት ጉዳት ካለመከሰቱም በላይ የገንዘብ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑንም ተገንዝበናል ካሉ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ለከንቲባ ከድር፣አብረዋቸው ለሚሰሩና ለመላው ቤተሰቦቻቸው ረጅም እጅሜ ከጤና ጋር ይስጥልን በማለት አባታዊ መልዕክታቸውን አጠናቀዋል። በመርሐ ግብሩ ኀላይ ካህናትና የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ያሬዳዊ ዝማሬን አቅርበዋል። ሊቃውንትም ቅኔ አበርክተዋል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ አርሲ-አቦምሳ ወረዳ ተገኝቶ ምዕመናንን አጽናና ጊዜያዊ ርዳታም አበረከተ።
  • “በአርሲ የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን እንሠራለን” የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች
  • ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በሀገረ ስብከቱ ለካህናት የሚሰጠውን ሥልጠና በጸሎትና በቡራኬ አስጀመሩ።
  • ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ተገኝተው የተጎዱ ወገኖችን የሚያጽናኑ በፁዐን አባቶችን መደበ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን የልዑካን ቡድን ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሰላም ሚኒስቴርና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያየ።

Archives

  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የሸገር ማረሚያ ቤት ታራሚዎች እውቀትና ጉልበታቸውን በማስተባበር ቤተክርስቲያን በማነጽ ላይ ናቸው። Link to: የሸገር ማረሚያ ቤት ታራሚዎች እውቀትና ጉልበታቸውን በማስተባበር ቤተክርስቲያን በማነጽ ላይ ናቸው። የሸገር ማረሚያ ቤት ታራሚዎች እውቀትና ጉልበታቸውን... Link to: በሀዋሳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ታህሳስ 19 የሚከበረው የመጋቤ ሐዲስ የቅዱስ ገብርኤልን በዓለ ንግሥ Link to: በሀዋሳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ታህሳስ 19 የሚከበረው የመጋቤ ሐዲስ የቅዱስ ገብርኤልን በዓለ ንግሥ በሀዋሳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ታህሳስ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top