የአዳማ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምህረት ካቴድራል 1ኛ ዓመት የቅዳሴ ቤት ክብረ በዓል ብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ በተገኙበት ተከበረ
ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም
ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀማዳዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ቡራኬ ተባርኮ የተመረቀው የአዳማ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምህረት ካቴድራል አንደኛ ዓመት የቅዳሴ ቤቷ ክብረ በዓል በዛሬዋ ዕለት፤
ብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ቋሚ አባልና የኢትዮጵያ ሃይማኖቶች ተቋማት የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሰብሳቢ በተገኙበት ተከብሯል።
በክብረ በዓሉም ላይም መልአከ ሣህል ቀሲስ ነጋሽ ሀብተ ወልድ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣የሀገረ ስብከቱ የየመምሪያው ክፍል ኃላፊዎች ፣ የገዳማት አድባራት አስተዳደሪዎች ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ካህናት ወዲያቆናት መምህራነ ወንጌል ፣ የሰንበት ት/ቤት ዘማርያን ማኅበራት: አባ ገዳዎችና አደ ስንቄዎች በርካታ ኦርቶዶክሳውያን ተገኝተዋል። ©ሐመረ ተዋሕዶ ሚዲያ