የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የደብረ ታቦር በዓል በምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከበረ።

August 21, 2026
ነሐሴ ፲፫ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በከፍተኛ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ከምታከብራቸው ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኝ ዓበይት በዓላት አንዱ የደብረ ታቦር በዓል ነው፡፡ ይህ በዓል በተለምዶ ቡሄ በመባል ይታወቃል፡፡
በምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የዳውሮ ኮንታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የገዳሙ አገልጋዮችና እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የደብረ ታቦር በዓል በታላቅ ድምቀት ተከበረ።
የደብረ ታቦር በዓል ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በታቦር ተራራ ብርሃነ መለኮቱን፣ ክብረ መንግሥቱን መግለጡን በማሰብ በየዓመቱ በድምቀት ይከበራል /ማቴ. ፲፯፥፩፤ ማር.፱፥፩፤ ሉቃ.፱፥፳፰/፡፡ በዚህ በዓል መለኮታዊ ክብሩ፣ የነቢያትና የሐዋርያት ምስክርነት ይተረጎምበታል፡፡
የገዳሙ የደብረ ታቦር በዓል አዘጋጅ ኮሚቴ ባቀረበው ሪፖርት መሠረት በዓሉ ሲከበር ዘንድሮ ለ53ኛ ጊዜ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ “የተሰባሰብንበት ዋና ዓላማው የደብረ ታቦርን በዓል ለማክበር ሲሆን የበዓሉ አከባበር ቀደም ባሉት ጊዜያት በገዳሙ ይኖሩ በነበሩ ጥቂት ዲያቆናትና የመነኮሳት አርድእት ደከመን ሰለቸን ሳይሉ በየዓመቱ በዳቦና ሻይ ከማክበር ተነሥቶ ፈቃደ እግዚአብሔር ተጨምሮበት ለበርካታ ዓመታት በታላቅ ድምቀት እየተከበረ አሁን ያለበት ደረጃ ደርሷል፡፡ ይህ ታላቅ በዓል መከበር ከጀመረ 53ኛ ዓመቱን” ይዟል፡፡
ሪፖርቱ አያይዞም በገዳማችን ይህ በዓል ሲከበር ተመሳሳይ ዓላማ ቢኖረውም ነገር ግን ከዚህም ባለፈ በገዳሙ የነበሩ አባቶችና ወንድሞች በተለያየ የሕይወት አጋጣሚ ከገዳሙ ሲወጡ በዚያው ርቀው እንዳይቀሩ ይህንን ገዳም እንደራሳቸው ቤት እንዲመለከቱ ለማድረግም ጭምር ሲሆን በፍቅር ይህን በዓል ሲታደሙ ከአዲሱ ትውልድ ጋር ለመተዋወቅና ለመቀራረብ መልካም አጋጣሚ የሚፈጥር መሆኑ በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡
በበዓሉ ላይ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የዳውሮ ኮንታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት መልእክት “ይህ በዓል በቤተክርስቲያናችን ትልቅ ሥፍራ የሚሰጠው የከፍታ በዓል ነው፤ ከፍ ያሉ ዝቅ፣ ዝቅ ያሉ ከፍ ያሉበት በዓል ነው፡፡ ሕያዋን ሙታን የተገናኙበት፣ ሙሴና ኤልያስ በመካከላቸው ሰፊ ዘመናት ያላቸውን እግዚአብሔር ያገናኘበት ጴጥሮስ፣ ዮሐንስ ያዕቆብና በዓል ነው፡፡ እግዚአብሔር እንዴት አድርጎ ሰውን እንደሚያገናኝ እናያለን፡፡ ይህም ቤተክርስቲያን የተለያዩ ሰዎችን በአንድነት እንደምታገናኝ የሚያሳይ ነውና በሌላ በኩል ይህ በዓል በአብነት ትምህርት ቤት የተማሪ በዓል ይባላል፤ ተማሪዎች ለምነው ስኮላርሺፕ የሰጣቸውን ሕዝብ የሚመግቡበት፣ የራሳቸውን ፍቅር ያሳዩበት በዓል ነው፡፡” ሲሉ ገልጻዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ባስተላለፉት መልእክት “በዛሬው በገዳማችን በሚከበረው በዓል ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ ስለተገኙ አመሰግናለሁ፡፡ በዚህ ገዳም በቀደሙት ዓመትት በየዓመቱ ተማሪዎች የደብረ ታቦር በዓል ያከብሩ ነበር፡፡ ዛሬም የገዳሙ ዲያቆናት የቀደሙትን መሠረት በማድረግ ሰው አስተባብረው በጋራ የሚያከብሩት፡፡ እግዚአብሔር ሰላሙን ሰጥቶ በሰላም እንድናከብር ያደረገ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን፣ የሰለላም በዓል ያድርግልን” ሲሉ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን ለመግለጽ የታቦር ተራራን የመረጠው፤ ትንቢትና ምሳሌውን ለመፈጸም ነው፡፡ ትንቢቱ፡- “ታቦር ወአርሞንኤም በስመ ዚአከ ይትፌስሑ ወይሴብሑ ለስምከ ታቦርና አርሞንኤም በስምህ ደስ ይላቸዋል” /መዝ. ፹፰፥፲፪/ በማለት ነቢዩ ዳዊት ትንቢት ተናግሮ ነበርና ጌታም ብርሃነ መለኮቱን በታቦር ተራራ በመግለጹ ይህ ትንቢት ተፈጽሟል፡፡ ምሳሌው፡- ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ ነው፤ ይኸውም መስፍኑ ባርቅ ሲሣራን በታቦር ተራራ ድል ነስቶታል /መሳ. ፬፥፬—፳፬/፡፡
የደብረ ታቦር በዓል በቤተክርስቲያናችን ከዋዜማው ጀምሮ እስከ በዓሉ ፍጻሜ ድረስ ማሕሌት ይቆማል፡፡ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ስለ በዓሉ የደረሰው “በታማኞችህ ነቢያት በሙሴና በኤልያስ ፊት የባሕርይ ልጅነትህን መሰከርኩልህ” የሚለው መዝሙር በመዘመር ለበዓሉ ልዩ ድምቀት ተሰጥቶት ይውላል፡፡ የአብነት ተማሪዎች እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ትምህርት ሃይማኖትን የሚማሩ ናቸውና ለሐዋርያት ነገረ መለኮቱን የገለጠ አምላክ እንዲገልጥላቸው በዓለ ደብረ ታቦርን በተለየ ድምቀት ያከብሩታል፡፡ በዚህም መሠረት በምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳምም በዓሉ በታላቅ ድምቀት ተከብሯል፡፡
©የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/
Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/pr000071.jpeg 299 448 eotceth https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg eotceth2026-08-21 04:35:102026-08-21 04:35:10የደብረ ታቦር በዓል በምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከበረ።
Search Search

Recent Posts

  • የደብረ ታቦር በዓል በምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከበረ።
  • ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ በባሕታዊ አባ ተስፋ ማርያም ሕልፈተ ሕይወት የተሰማቸውን ኅዘን በመግለጽ አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል፤ የብፁዕነታቸው አባታዊ መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል::
  • ብፁዕ ጠቅላዬ ሥራ አስኪያጂና ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው ቤተክርስቲያን የምታከናውናቸውን የልማት ሥራዎች አፈጻጸምን ተዘዋውረው ተመለከቱ።
  • የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት 14ኛ ዓመት መታሰቢያ በዓል ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድሥት ሥላሴ ካቴድራል በመከበር ላይ ይገኛል።
  • ስምከ ሕያው ዘኢመውት ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

Archives

  • August 2026
  • July 2026
  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church
  • Link to Facebook
Link to: ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ በባሕታዊ አባ ተስፋ ማርያም ሕልፈተ ሕይወት የተሰማቸውን ኅዘን በመግለጽ አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል፤ የብፁዕነታቸው አባታዊ መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል:: Link to: ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ በባሕታዊ አባ ተስፋ ማርያም ሕልፈተ ሕይወት የተሰማቸውን ኅዘን በመግለጽ አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል፤ የብፁዕነታቸው አባታዊ መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል:: ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ በባሕታዊ አባ ተስፋ ማርያም...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top