የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

በክልል ትግራይ ካሉ ብፁዓን አባቶች ጋር የተፈጠረውን ችግር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመፍታት እየተሠራ እንደሆነ የሰላም ልዑኩ ገለጸ ።

June 14, 2023

ሰኔ ፯ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ዓ.ም
*****
አዲስ አበባ -ኢትዮጵያ
“””””””””””””””””””””

የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ አሜን !!!

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላምና የስምምነት ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የካቲት 7 ቀን 2015 ዓ.ም በቅዱስነታቸው ፊርማ ባወጣው ደብዳቤ በትግራይ ክልል የተከሰተውን ጦርነት ተከትሎ በካህናት ፣ በምእመናን ፣ በገዳማትና በአድባራት ላይ ስለደረሰው ጉዳት የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን በይፋ መግለጹ ይታወሳል።

በግንቦት ወር ባካሄደው የርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤም በክልል ትግራይ የሚገኙ አባቶቻችን የሚያነሱትን ቅሬታ በተመለከተ ጉዳዩ በውይይትና በህግ የሚፈታበት መንገድ እንዲፈጠር ቀደም ሲል በቅዱስ ሲኖዶስ የተሰየመው ኮሚቴ ሥራውን እንዲቀጥል መመሪያ ሰጥቶ ችግሩ በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ውሳኔ አስተላልፏል።

የተቋቋመው ኮሚቴም ችግሩ በሰላማዊ መንገድና በስምምነት መቋጨት የሚችልበትን አቅጣጫ በመቀየስ በርካታ የቅድመ ውይይት ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል።ወደፊትም የቅዱስ ሲኖዶስን መመሪያ በመቀበል ችግሩ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በተከተለ አግባብ መፍትሔ እንዲያገኝ ለማድረግ የሚቻለውን ሁሉ ለማድረግ ደፋ ቀና እያለ ይገኛል።

በክልል ትግራይ የሚገኙ ብፁዓን አባቶቻችን የሚያነሷቸው ጥያቄዎች ሁሉ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በተከተለ አግባብ ለመፍታት ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን የምታደርገውን የእናትነት እንቅስቃሴ በማዛባት ልዩነት እንዲሰፋና የቤተክርስቲያናችን ተቋማዊ አንድነት እንዲናጋ ሌት ተቀን የሚጥሩ አንዳንድ የሚዲያ ተቋማትም ችግሩ ዘለቄታዊ መፍትሔ እንዳያገኝ ሆን ብለው እየሠሩ እንደሚገኙ እንገነዘባለን።

ይሁንና ችግሩ የሚፈታው በእልህና በቁጣ ልዩነትን በማስፋትና በመራራቅ ሳይሆን በሰከነ መንገድ በሰለጠነ አስተሳሰብና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን መሠረት ባደረገ በግልጽ ውይይት መሆኑን በመገንዘብ የችግሩ መነሻዎችን አሁን ያሉበትን ደረጃና ወደፊት ሊደረግ የሚገባ የሚባሉ ነጥቦችን በመለየት በውይይት መፍታትና በመጨረሻ ጉዳዩን በእርቀ ሰላም ማጠቃለል እንደሚገባም ኮሚቴው በጽኑ ያምናል።

ስለሆነም በክልል ትግራይ የሚገኙ ብፁዓን አባቶቻችን ቀደምት አባቶቻችን ለሃይማኖታቸው አንድነትና መስፋፋት እንዲሁም ለቀኖና ቤተ ክርስቲያን መጠበቅ የከፈሉትን መስዋዕትነት መሠረት በማድረግ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችሁ አንድነትና ሉዓላዊነት በጽናት በመቆም ተፈጠሩ የሚባሉ ችግሮችን ሁሉ በዝርዝር ለማቅረብ ለውይይት ዝግጁ እንድትሆኑ መልእክታችንን እያስተላለፍን የምታቀርቧቸውን የውይይት ነጥቦች መሠረት በማድረግ ችግሮቹን በስምምነት ለመፍታት ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ዝግጁ መሆኗን እንወዳለን።

በዚህም የውይይትና የሰላም መልእክታችን ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ያስተላለፈችውን ጥሪ በመቀበል በአጭር ጊዜ ውስጥ ለውይይትና ለስምምነት ዝግጁ እንድትሆኑ ጥሪያችንን እያስተላለፍን በቅርብ ቀናት ውስጥ የሰላም ልዑኩ ለውይይት ወደ ክልል ትግራይ መቀሌ ከተማ ስለሚጓዝ በጋራ በምናደርጋቸው ቦታና ጊዜ የውይይትና የስምምነት ጉባኤ የሚደረግ ይሆናል።

የፌዴራል መንግሥትና የክልል ትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርም ችግሩ በሰላማዊ መንገድና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በጠበቀ መልኩ መፍትሔ ያገኝ ዘንድ የሚደረገውን ጥረት ሁሉ በመደገፍና ለውይይቱ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግልን በዚሁ አጋጣሚ መልእክታችንን ለማስተላለፍ እንወዳለን።

አምላካችን እግዚአብሔር ኢትዮጵያ ሀገራችንንና ሕዝባችንን ይባርክ !

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
የሰላምና የስምምነት ኮሚቴ

ሰኔ 5 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

 

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/abune-henok-intro.jpg 452 400 tc https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg tc2023-06-14 10:51:032023-06-14 10:51:03በክልል ትግራይ ካሉ ብፁዓን አባቶች ጋር የተፈጠረውን ችግር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመፍታት እየተሠራ እንደሆነ የሰላም ልዑኩ ገለጸ ።
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: በትግራይ ክልል ከሚገኙ አባቶች ጋር ውይይት ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተጠናቀቀ። Link to: በትግራይ ክልል ከሚገኙ አባቶች ጋር ውይይት ለማድረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተጠናቀቀ። በትግራይ ክልል ከሚገኙ አባቶች ጋር ውይይት ለማድረግ... Link to: ወቅታዊ መልዕክት Link to: ወቅታዊ መልዕክት ወቅታዊ መልዕክት
Scroll to top Scroll to top Scroll to top