ብፁዓን አባቶች በጥቁር አንበሳ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በመገኘት ሕሙማንን ጎበኙ

መጋቢት 30/7/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የትንሳኤ በዓልን በማስመልከት በጥቁር አንበሳ እስፔሻላይዝድ ኦስፒታል በመገኘት በእመም ላይ ያሉ ሕሙማንን ጎብኝተው ማዕድ አጋሩ፣የቁሳቁስና የገንዘብ ድጋፋ አደረጉ።
ጉብኝቱ የተካሄደው የትንሳኤ በዓል መንፈሳዊ ትርጉምን በተግባር ለማሳየት ሲሆን፣ በበዓሉ ወቅት በሕክምና ላይ ያሉ ወገኖች እንዳይረሱ እና ከማህበረሰቡ ጋር እንደተገናኙ እንዲሰማቸው የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት ሕሙማኑን በማበረታታት፣ የህክምና ባለሙያዎችን ማመስገንና መንፈሳዊ ድጋፍ ማድረግ የቤተክርስቲያን ተቀዳሚ ተግባሯ መሆኑን ገልጸዋል።
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት
ዋና ሥራ አስኪያጅ በበኩላቸው የታመመውን መጠየቅና የታረዘውን ማልበስ ክርስቲያናዊ አስተምህሮ መሆኑን ገልጸው፣ ሕሙማኑ ፈጣን ፈውስ እንዲያገኙ እግዚአብሔርን በጸሎት ጠይቀዋል። የእንኳን አደረሳችሁ መልህክታቸውንም አስተላልፈዋል።ዶክተር ራኤል የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አመሰራረት እና የሚሰጡትን አገልግሎቶች በመግለጽ፣ “አባቶቻችን በተጣበበ ሰዓት በዚህ ስፍራ መገኘታቸው ለታካሚዎቻችን ተስፋ ሲሆን ለእኛ ደግሞ ታላቅ ማበረታቻ ነው” ብለዋል።
በዚሁ ጊዜ ለበዓል መዋያ የሚሆን 500,000 (አምስት መቶ ሺህ) ብር እና የተለያዩ የንጽሕና መጠበቂያ ቁሳቁሶች ድጋፍና ከማድረጋቸውም በላይ ለሕሙማኑ ማዕድ አጋርተዋል።
በጉብኝቱ ወቅት ከብፁዓን አባቶች ጋር ዶክተር አካለ ወልድ ተሰማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙሃን ሥራ አስኪያጅ፣ ሊቀ ስዩማን እስክንድር ገብረ ክርስቶስ የቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደር ዋና ሥራ አስኪያጅና የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ፣መጋቤ ካህናት አባ ሃብተጊዮርጊስ አስራት የገዳማት መምሪያ ኃላፊ እንዲሁም መላከ ኃይል አባ አፈወርቅ ዮሐንስ የሦስቱ ክፍላተ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ተገኝተዋል።
የጥቁር አንበሳ ኦስፒታል አስተዳደር በተደረገው ጉብኝትና ድጋፍ ከፍተኛ ደስታ እንዳላቸው ገልጸው፣ ይህ ዓይነት ማህበራዊና መንፈሳዊ ድጋፍ ለሕሙማን ትልቅ ኃይል እንደሚሰጥ አመልክተዋል።
በመጨረሻምብፁዓን አባቶች እና የመንበረ ፓትሪያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ልዑካን በሕመምላይ የሚገኙትን ታማምዎችን ተዘዋውረው በመጠየቅና ለሁሉም ፀሎት በማድረግ ጉብኝቱ ፍጻሜውን አግኝቶአል ።