የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ብፁዕ አቡነ አብርሃም ወቅታዊ የቤተክርስቲያንን ሁኔታ አስመልክቶ የሰላም ጥሪ አተስላለፉ።

July 20, 2023

ሐምሌ ፲፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም አዲስ አበባ

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወቅታዊ የቤተክርስቲያናችንን ሁኔታ አስመልክቶ ዛሬ ሐምሌ ፲፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ/ም ከቀትር በኋላ በጽ/ቤታቸው ልዩ መግለጫ ተሰጥተዋል።

ብፁዕነታቸው ባስተላሐፉት የሰላም ጥሪ በክልል ትግራይ አህጉረ ስብከት ለሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት አንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያንን በጽናት ለማገልገል በጋራ የገቡትን ቃልኪዳን በማስታወስ በተደጋጋሚ የተደረገላቸውን የሰላም ጥሪ እንዲቀበሉ ደግመው አሳስበዋል።

ብፁዕነታቸው እንደገለጹት ከሆነ ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በፌደራል መንግስትና በትግራይ ክልል፣ በትግራይ ክልልና በአማራ ክልል ያለውን ውጥረት ለማርገብ ጥረት እናድርግ የሚል የሰላም መልዕክት ባስተላለፍንበት ወቅት በክልል ትግራይ አህጉረ ስብከት የተመደቡ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ትግራይ ሰላም መሆኗንና ደም ወደሚፈስባቸው ሌሎች አካባቢዎች እንድናተኩር ሲያሳስቡን ቆይተዋል ብለዋል።

ይሁን እንጂ በትግራይ ክልል የደረሰው ጉዳት ቤተክርስቲያንን እጅግ ያሳዘነ በመሆኑ የመልሶ ማቋቋም ሥራውን በጋራ መሥራት ይቻል ዘንድ መፍትሔው ተቀራርቦ በአባትነት መንፈስ መመካከር እንጂ በሕገ ቤተክርስቲያን ከተደነገገው ውጪ ኤጲስ ቆጶሳትን መሾም ባለመሆኑ ለውይይት በራቸውን እንዲከፍቱ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

በትግራይ ክልል የሚገኙ ሊቃውንት የቤተክርስቲያናችንን ቀኖናና ሥርዓት መሠረት በማድረግ ከቤተክርስቲያን ጎን እንዲቆሙ ጥሪአችንን እናስተላልፋለን ያሉት ብፁዕነታቸው በትግራይ አህጉረ ስብከት የተጀመረውንም ቤተክርስቲያንን የመክፈል አዝማሚያ በመጽሐፍ መሠረትነት እንዲሞግቱና በክልሉ የሚገኙ አባቶች እያካሔዱት ካለው ጠቃሚነት የሌለው ተግባር እንዲቆጠቡ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ አሳስበዋል።

የፌደራል መንግሥትም ሆነ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሰተዳደር መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አንገባም በሚል አመክንዮ በክልል ትግራይ አህጉረ ስብከት የተመደቡ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን በተመለከተ ዝምታን ቢመርጡ በቤተክርስቲያናችን ላይ በሚደርሰው መከፈል ከታሪክ ተጠያቂነት እንደማይድኑ በመግለጽ የማሸማገል ተግባራቸውን እንዲወጡ አባታዊ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

በመጨረሻም ምእመናን በዚህ አስጨናቂ ወቅት ያላቸውን ቅሬታ ሁሉ ትተው ከቤተክርስቲያን ጎን እንዲቆሙ የቤተክርስቲያናችን ወዳጆችም እንደ እስከአሁንኑ ሁሉ ቤተክርስቲያንን እንዲያግዙ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/photo_2023-07-20_21-01-48-cover.jpg 447 400 tc https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg tc2023-07-20 19:05:372023-07-20 19:05:37ብፁዕ አቡነ አብርሃም ወቅታዊ የቤተክርስቲያንን ሁኔታ አስመልክቶ የሰላም ጥሪ አተስላለፉ።
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: አዲስ ለሚሾሙት ኤጲስ ቆጶሳት የጸሎተ አስኬማ ሥነሥርዓት ተከናወነ። Link to: አዲስ ለሚሾሙት ኤጲስ ቆጶሳት የጸሎተ አስኬማ ሥነሥርዓት ተከናወነ። አዲስ ለሚሾሙት ኤጲስ ቆጶሳት የጸሎተ አስኬማ... Link to: በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት የ፲ ዓመት ስልታዊ እቅድ ዙሪያ ለሁለት ቀናት የተካሄደው የምክክር ጉባኤ ተጠናቀቀ:: Link to: በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት የ፲ ዓመት ስልታዊ እቅድ ዙሪያ ለሁለት ቀናት የተካሄደው የምክክር ጉባኤ ተጠናቀቀ:: በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት የ፲ ዓመት ስልታዊ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top