የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በእስራኤል ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የተመራ ልዑክን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ፡፡

February 13, 2025

የካቲት 6 ቀን 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
+ + +
ብፁዕ ወቅዱስነታቸው በዛሬው ዕለት የእሥራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ሚኒስትር የሆኑትን ክብርት ሻረን ሃስኬል፣ በኢትዮጵያ የእሥራኤል አምባሳደር ክቡር አብርሃም ንጉሤን እና ከፍተኛ የሥራ ሓላፊዎችን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡ ክብርት ምክትል ሚኒስቴር ሻረን ሃስኬል በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ለእርሳቸውና ለመጡት ልዑካን በተደረገላቸው የክብር አቀባበል መደሰታቸውን ገልጸው እሥራኤል የምትገኝበትን ወቅታዊ ሁኔታ፤ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጋር ያለውን ግንኙነት አጠናክሮ ለማስቀጠል በእሥራኤል ሀገር መንግሥት በኩል ያለውን ፍላጎት አስረድተዋል፡፡

ቅዱስነታቸውም የሃይማኖት መሠረት የሆነችው እሥራኤል ከኢትዮጵያ ጋር ያላት ግንኙነት ከዘመነ ኦሪት ጀምሮ ሰፊ ትስስር ያለው መሆኑን በማስታወስ ዓለም በልዩ ልዩ መልኩ እየተፈተነች ባለበት ወቅት በእሥራኤልና ፍልስጥኤም መካከል ተከስቶ በቆየው ጦርነት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን ገልጸው በኢየሩሳሌምና አካባቢዋ የሚገኙ ገዳማት፣ አብያተ ክርስቲያናት፣ አብያተ እምነት እና ታሪካዊ ቦታዎች በጦርነቱ ጉዳት እንዳይርስባቸው ጥበቃ በማድረግ የእሥራኤል መንግሥት የወሰደውን ጥንቃቄ በማድነቅ አመስግነዋል፡፡

ቅዱስነታቸው ከእሥራኤል ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ባደረጉት ሰፊ ውይይት ቤተ ክርስቲያናችን ከእሥራኤል መንግሥት ጋር በጋራ የምታከናውናቸው ተግባራትን የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕግጋት ባከበረ መልኩ ማዕከላዊ አሠራርን በመጠበቅ አጠናክሮ ማስቀጠል በሚቻልበት ዙሪያ ከመግባባት ላይ ተደርሷል፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ አርሲ-አቦምሳ ወረዳ ተገኝቶ ምዕመናንን አጽናና ጊዜያዊ ርዳታም አበረከተ።
  • “በአርሲ የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን እንሠራለን” የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች
  • ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በሀገረ ስብከቱ ለካህናት የሚሰጠውን ሥልጠና በጸሎትና በቡራኬ አስጀመሩ።
  • ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ተገኝተው የተጎዱ ወገኖችን የሚያጽናኑ በፁዐን አባቶችን መደበ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን የልዑካን ቡድን ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሰላም ሚኒስቴርና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያየ።

Archives

  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የአክትስ ቸርች ኦፍ ሱዲን የሥራ ኀላፊዎችን   በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ። Link to: ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የአክትስ ቸርች ኦፍ ሱዲን የሥራ ኀላፊዎችን   በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ... Link to: መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ Link to: መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
Scroll to top Scroll to top Scroll to top