የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ለተመደቡት ለመልአከ ብርሃን መምህር ሰሎሞን በቀለ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ነሐሴ ፰ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ምመልአከ ብርሃን መምህር ሰሎሞን በቀለ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው መመደባቸውን ተከትሎ ንቡረ እድ ኤልያስ አብርሃ በመንበረ ፓትርያርክ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ መልአከ ሰላም ዶክተር አባ ቃለጽድቅ ሙሉጌታ በመንበረ ፓትርያርክ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ሓላፊ፣ የሀገረ ስብከቱ የሥራ ሐላፊዎች፣ የክፍላተ ከተማ ቤተ ከህነት ሥራ አስኪያጆች፤ የሀገረ ስብከቱና የክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ሠራተኞች በተገኙበት በሀገረ ስብከቱ አደራሽ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
መልአከ ብርሃን መምህር ሰሎሞን በቀለ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ሲመደቡ፤ ፍትሐዊ የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት፤ ስር ነቀል ለውጥ በማምጣት ፍትሕና ርትዕ እንዲያሰፍኑ መሆኑን ተገልጻል።
በአቀባበሉ ሥነ ሥርዓት የተገኙት፤ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመንፈሳዊ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር ንቡረ እድ ኤልያስ አብርሃ፣ ቀደም ሲል ፈተና ያለፉት መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለ ወደ ሀገረ ስብከቱ በዋና ሥራ አስኪያጅነት ሲመደቡ በሥራና በአሠራር ስር ነቀል የሆነ ለውጥ እንዲያመጡ ተብሎ መሆኑን ተናግረዋል።
የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተመደቡት መልአከ ብርሃን ሰሎሞን በቀለም፤ በቤተ ክርስቲያን አባቶች የተጣለባቸውን አደራ ለመወጣት፤ ብቻቸውን ሳይሆን በጋራ መሥራት ሲቻል መሆኑን በመግለጽ በክብር እንደገቡ በክብር እንዲወጡ በጸሎት አግዙኝ ብለዋል።
በአቀባበሉ መርሐ ግብር፤ ቅኔ በሊቃውንት፣ የእንኳን ደኅና መጡ እና የመልካም ሥራ ምስክርነት በሀገረ ስብከቱ እና በክፍለ ከተማው ሠራተኞች የቀረበ ሲሆን አገባባቸው ብቻ ሳይሆን አወጣጣቸውም በመልካም እንዲሆን ተመኝተዋል።
መልአከ ብርሃን መምህር ሰሎሞን በቀለ የቦሌ ገርጂ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርግስ እና ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ን በስብከተ ወንጌል ።
የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል፣ የደብረ ሰላም ቦሌ መድኃኔ ዓለም ካቴድራል፣ የደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተክርስቲያን እና የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ቤተ ክርስቲያን ዋና ፀሐፊ በመሆን ያገለገሉ ሲሆን፤
የቦሌ ሰሚት መካነ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን እና የቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ዋና አስተዳዳሪ በመሆን ያገለገሉ አባት ናቸው።
በቀጣይ ከሱባኤ በኋላ ከአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎችና የሥራ ሐላፊዎች እንዲሁም ከሰበካ ጉባኤ አባላት ጋር የሥራ ትውውቅ መርሐ ግብር እንደሚኖር በአቀባበል መርሐ ግብሩ ተጠቁሟል።
©የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/