የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የ2016 ዓ.ም የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት የቅዱስ ፓትርያርኩ የእንኳን አደረስዎ መርሐ ግብር በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ተከናወነ።

January 8, 2024

ታኅሣሥ ፳፱ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
“””””””””””””””””””””””””””””””
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
——————-

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖትን እንኳን ለ2016 ዓ.ም የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረስዎ ለማለት በተዘጋጀው መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ; ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ;ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ክቡር ሊቀ ትጉሃን ታጋይ ታደለ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጸሐፊ፣ ክቡር ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የየመምሪያውና የድርጅት ኃላፊዎች፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ተገኝተዋል።

በመርሐ ግብሩ ጸሎተ ወንጌል የደረሰ ሲሆን የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ደቀ መዛሙርት ያሬዳዊ ዜማ አሰምተዋል።
በማስከተልም የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች እና የጋሞ ብሔረሰብ ዘማርያን መዝሙር አቅርበዋል።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ለ2016 ዓ.ም የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት ቅዱስ ፓትርያርኩን የእንኳን አደረስዎ በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸውም በዚህች ዕለት ቅዱሳን አባቶቻችን እንዳሉት ‹‹በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው፤ በቅዱሳን ላይ የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰው ሆኗልና ኑ ይህን ድንቅ እዩ፤ ስለተገለጠልን ምሥጢር ምስጋና አቅርቡ፤ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና ቃል ተዋሕዷልና ጥንት የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፣ ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት፡፡ የማይታወቅ ተገለጠ፣ የማይታይ ታየ፣ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ በእርግጥ ሰው ሆነ›› እያልን ሐሴት በፍስሐ የጌታችን የልደት በዓል እያከበርን እንገኛን ያሉ ሲሆን፡፡ ስለ ሀገራችን ሰላምና ስለ ቤተክርስቲያናችን አንድነት ቅዱስነታቸው እና ቅዱስ ሲኖዶስ በሚወስናቸው ማናቸውም ውሳኔዎች ለማስፈጸም ያላቸውን ቁርጠኝነት በመግለጽ ቅዱስነታቸውን ለብርሃነ ልደቱ በዓል በሰላም አደረስዎ ብለዋል፡፡

በዝግጅቱ በሊቃውንት ቅኔ የቀረበ ሲሆን ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቅዱስነታቸውን እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት አደረስዎ በማለት የመልካም ምኞት መግለጫ አስተላልፈዋል።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም “ሰላም በምድር ለሰው ልጅ በጎ ፈቃድ ” በሚል ቅዱስ ቃል መነሻነት ሰብአሰገል ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስጦታ እንዳቀረቡ አስታውሰው በዓሉ ለምድር ሰላም የታወጀበት ታላቅ በዓል ነው ብለዋል። እያንዳንዳችን በተሰለፍንበት ዘርፍ ቤተክርስቲያንን ማገልገል እንድንችል የቅዱስነትዎ ቡራኬና ጸሎት አይለየን ብለዋል። ብፁዕነታቸው በቦሌ ደብረ ሣሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል በልደት በዓል ዋዜማ የተከበረውን በኢትዮጵያዊዉ ጃንደረባ ትውልድ የተሰናዳውን “የአእላፋት ዝማሬ” ልዩና ቤተ ክርስቲያንን የሚመጥን ነው ይህም በቅዱስነትዎ በዘመነ ፕትርክናዎ የተከናወነ በመሆኑ በሚሰጡን መመሪያ አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል።

በክብረ በዓሉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ባስተላለፉት መልዕክት እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ በማለት በዓሉን ለማክበር በሥፍራው ለተገኙ ትምህርት ሰጥተዋል።

ቅዱስነታቸው አዳምና ሔዋን ዕፀ በለስን በመብላታቸው ምክንያት በሞተ ሥጋ ላይ ሞተ ነፍስ በርደተ መቃብር ላይ ርደተ ገሃነመ እሳት ተፈርዶባቸው 55ዐዐ ዘመን በመከራ መቆየታቸው ይታወቃል፡፡ ነገር ግን አዳምና ሔዋን ዕፀ በለሱን ከበሉ በኋላ እግዚአብሔር መሐሪ መሆኑን በመረዳት ንስሐ ገብተው ንስሐቸውን ሲጨርሱ እግዚአብሐር ተስፋ ሰጥቷቸዋል፤ ተስፋቸውም “በሐሙስ ዕለት ወበመንፈቃ ለዕለት እትወለድ እም ወለተ ወለትከ ” 55ዐዐ ዘመን ሲፈፀም ከልጅ ልጀህ ተወልጄ አድንሃለሁ ብሎ ተስፋ ስለሰጣቸው ይሄን ተስፋ ለመፈፀም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ከድንግል ማርያም በመወለዱ ምክንያት አድርገን በዓሉን በታላቅ ድምቀት እያከብርን እንገኛለን ብለዋል።

ነጻ ፈቃድ ቢኖረንም በምርጫችን ልንጠነቀቅ ይገባል ለሀገር ሰላም እና አንድነት ልንሠራ ይገባል ብለዋል።
ቅዱስነታቸው እርሳቸው የተገኙበት በቦሌ ደብረ ሣሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል በልደት በዓል ዋዜማ የተከበረውንና በኢትዮጵያዊዉ ጃንደረባ ትውልድ የተሰናዳውን “የአእላፋት ዝማሬ” በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ የተሰናዳ ነው ያሉ ሲሆን የሰላም መዝሙር የተዘመረበት ነው ብለዋል።

በመጨረሻም ቅዱስነታቸው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጥተው በጸሎት መርሐ ግብሩ ፍጻሜ አግኝቷል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የሰላማችን ሰንደቅ ዓላማ የሆነው ወልድ ወይም ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ለኛ ተወለደልን Link to: የሰላማችን ሰንደቅ ዓላማ የሆነው ወልድ ወይም ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ለኛ ተወለደልን የሰላማችን ሰንደቅ ዓላማ የሆነው ወልድ ወይም ወልደ... Link to: የብፁእ አቡነ ጴጥሮስ ሐዋርያዊ ጉዞ በቤተ ክርስቲያን ሕግ እና ሥርዓት መሠረት የተፈቀደ ነው። Link to: የብፁእ አቡነ ጴጥሮስ ሐዋርያዊ ጉዞ በቤተ ክርስቲያን ሕግ እና ሥርዓት መሠረት የተፈቀደ ነው። የብፁእ አቡነ ጴጥሮስ ሐዋርያዊ ጉዞ በቤተ ክርስቲያን...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top