የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

፵፪ ኛው ዓለምአቀፍ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ

October 20, 2023

ለ፵፪ ኛ ጊዜ የሚካሔደው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዓለም አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የተዋጣለት፣የተሳካና ውጤታማ በሆነ መልኩ መከናወን ይችል ዘንድ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎቹ በሚገባ ታቅደው፣ ለእያንዳንዱ ተግባር አስፈጻሚና ፈጻሚ አካል ተቀምጦለት የተከወነ ከመሆኑም በላይ የእያንዳንዱ ኮሚቴ የሥራ አፈጻጸምና አጠቃላይ የቅድመ ዝግጅት ሥራው አፈጻጸም በብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሚመሩት አስተዳደር ጉባኤ ተገምግሞ ማስተካከያ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ከተስተካከሉና ከታረሙ በኋላ ወደ ተግባር እንዲለወጡ ተደርጓል፤ ይህም በመደረጉ እያንዳንዱ የቅድመ ዝግጅት ሥራ ያማረና የተዋበ እንዲሆን ማድረግከመቻሉም በላይ በአፈጻጸም ደረጃም ውጤት የተመዘገበበት መሆን ችሏል።

ጉባኤው ውጤታማ ይሆን ዘንድ እግዚአብሔር እንዲረዳን በየዕለቱ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ጸሎትና ቡራኬ ተከፍቶ በቅዱስነታቸው ሊቀ መንበርነትና መመሪያ መሠረት እየተካሄድ ይገኛል ፡፡

በተለይም ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ጉባኤውን ፍትሐዊ በሆነ መልኩ በመምራታቸው የሰዓት መዛነፍና የተንዛዛ ሪፖርት እንዳይቀርብ ማድረግ ያስቻለ ሲሆን ከመርሐ ግብር ውጪ የሆኑና መስመራቸውን የሳቱ እንዲሁም ከእውነተኝነት የራቁ ሪፖርቶችን በማረቅ ሐቁ በግልጽ እንዲቀመጥ ያደረጉበት ጥረትም የብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁን የጉባኤ አመራር ጥበብና ብቃት ቁልጭ አድርጎ ያሳየ ተግባር ሆኖ ተመዝግበዋል። ጉባኤውም በተደጋጋሚ ጊዜ ይህን ሐቅ በጭብጨባ ሲገልጽ ተስተውሏል።

ሌላውና በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ዘመነ ሢመት ሥር ነቀል ማስተካከያ የተደረገበት ከዚህ በፊት ተጀምሮ መቀጠል የተሳነው ብዙዎች በየዓመቱ በሚካሔደው ጉባኤ ሲተቹት የሚሰማው ውይይት ለምን አይደረግም? የገንዘብ ሪፖርት ብቻ ነው የሚሰማው፣ ወዘተ የሚሉ ጥያቄዎችን የመለሰና በቡድን የተደረገ ውይይትን በጋራ ማብራሪያ የሚሰጥበት አሠራር ተጠናክሮ እንደገና የተጀመረው በብፁዕ አቡነ አብርሃም የአመራር ዘመን እንደሆነ እርግጥ ነው።

በዘንድሮ ዓለም አቀፍ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይም ልዩ ልዩ ወቅታዊ ጥያቄዎችን በማንሣት ውይይት ቢቀር ጥሩ ነው የሚል ዐሳብ ያነሡ የነበሩ ብዙዎች ቢሆኑም ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ግን ውይይት ሊፈራ አይገባውም። መለመድ አለበት። ችግሮች መፍትሔ የሚያገኙት በውይይት ነው።ስለዚህ ውይይት መካሔድ አለበት የሚል ጽኑዕ አቋም በማራመዳቸው የጋራም የቡድንም ውይይት በ፵፪ ኛው ዓለም አቀፍ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ እንዲካሔድ በአስተዳደር ጉባኤ ተወስኖ በመርሐ ግብሩ ተካቶ እነሆ ተፈጻሚ የሚሆንበት ጊዜ ሰሌዳ ላይ ደርሰናል።

በሚደረገው የቡድንም ሆነ የጋራ ውይይት ችግሮቻችንን የምንመለከትበት፣ለችግሮቻችን መፍትሔ የምንሰጥበት ሁኔታ እንደሚፈጠርም በዛሬው ዕለት በተጀመረው የውይይት መርሐ ግብር ላይ የተነሡት ዐሳቦችና ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የተሰጡት ማብራሪያዎች በቂ ማሳያዎች ናቸው። በቀሪው ጊዜም ይህን መሰል ገንቢና አስተማሪ ዐሳቦችን በሚገባ በማንሸራሸር በተቋም ደረጃ መፍትሔ የሚፈለግበትን መንገድ በመጠቆም በጉባኤው ላይ የተነሡ ዐሳቦችን መሠረት በማድረግ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውሳኔ የሚያርፍበትን ሁኔ ታ በማመቻቸት ቢያንስ በዚህ ዓመት ችግሮቻችንን በውል ተገንዝበን ከችግሮችን መውጣት በመጀመር ቅድስት ቤተክርስቲያናችንን መታደግ እንድንጀምራለን የሚል ተስፋ አለን።

በአጠቃላይ በዘንድሮ ጉባኤያችን ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ እስከ ጉባኤው መገባደጃ ቀን ድረስ የተመዘገቡ ውጤታማ ተግባራትን እውቅና መስጠት ተገቢ ስለሆነ ጉባኤው ያማረና የተሳካ እንዲሆን ከፍተኛ ጥረት ያደረጉት ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዶ/ር የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ፣በልዩ ልዩ ኮሚቴዎች በመታቀፍ ውጤታማ ሥራ ላከናወናችሁ የኮሚቴ አባላት፣ለጉባኤው ሞገስ በመሆን ለሰነበታችሁ ለመላው ጉባኤ አባለት ምስጋና ሊቸራችሁ ይገባል።

ከሁሉ በላይ ዘመኑን የሚመጥን አባታዊ መልዕክት በማስተላለፍ፣ በጸሎት በመክፈትና በመዝጋት ፣አባታዊ ምክርና ትምህርት በመስጠት በትዕግሥት ጉባኤውን ሲመሩ የሰነበቱት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ቅድስት ጸሎትዎና ቡራኬዎ ለጉባኤያችን ሞገስ ሆኖታልና ዘወትር ቡራኬዎ እንዳይለየን እንጸልያለን።

“ልዑል እግዚአብሔር ጉባኤያችንን በሰላም ያስጨርሰን! ”

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ጥቅምት ፱ ቀን ፳፻ ፲ወ ፮ዓ.ም
አዲስ አበባ -ኢትዮጵያ

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/favicon.png 169 151 tc https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg tc2023-10-20 08:54:402023-10-20 08:54:40፵፪ ኛው ዓለምአቀፍ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ለሰ/ት/ቤቶች መማሪያነት የተዘጋጀውን ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ ለማድረግ የሁሉም ርብርብ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ። Link to: ለሰ/ት/ቤቶች መማሪያነት የተዘጋጀውን ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ ለማድረግ የሁሉም ርብርብ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ። ለሰ/ት/ቤቶች መማሪያነት የተዘጋጀውን ሥርዓተ ትምህርት... Link to: ፵፪ ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በተመረጡ አሥር የውይይት ነጥቦች ዙሪያ ውይይት እየተደረገ ይገኛል:: Link to: ፵፪ ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በተመረጡ አሥር የውይይት ነጥቦች ዙሪያ ውይይት እየተደረገ ይገኛል:: ፵፪ ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በተመረጡ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top