የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ከወደቅንበት የራስን ጥቅም የማሳደድ አዚም ወጥተን የቤተ ክርስቲያንን ህልውና ሊያጸና የሚችለውን ሥራ እያስቀደምን ማገልገል የሁላችንም ውሳኔ መሆን እንዳለበት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አሳሰቡ።

April 17, 2023

ሚያዝያ ፱ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ዓ.ም
“””””””””””””””””””””””””””
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
******
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዛሬ ሚያዝያ ፱ቀን ፳፻ ፲ወ፭ዓ.ም በጠቅላይ ቤተክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ በተካሄደው የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር ላይ ያስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል።

*ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሀይማኖት፤

*ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤

*ክቡር ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን የጠቅላይ ቤተክህነት ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ፤

*ክቡራን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የመምሪያ ኃላፊዎችና የየድርጅቶቹ ኃላፊዎች፤

*ክቡር ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ ጸጋዬ የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤

*ክቡር ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጠቅላይ ጸሐፊ፤

*ክቡራን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ፤

*ክቡራን የቤተክርስቲያናችን ማኅበራት አመራሮች፤
*ክቡራንና ክቡራት

ከሁሉ አስቀድሞ ቡራኬዎ ይድረስኝ እያልኩ የእንኳን አደረሰዎ መልዕክት እንዳቀርብ እንዲፈቀድልኝ በታላቅ ትህትና እጠይቃለሁ።

“በአማን ተንሥአ እግዚእነ፤ በእውነት ጌታ ተነስቷል”ሉቃ 24፥34

ከሁሉ አስቀድሞ አምላካችን እግዚአብሔር ባለፉት ወራት በሀገራችንም ሆነ በቤተክርስቲያናችን የተከሰተውን ፈተና አሳልፎ ማዕበሉን ገቶ ከዚህ ስላደረሰን ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን እያልሁ ቅዱስነትዎ በሆነው ሁሉ በሀገርም ሆነ በቤተክርስቲያን ላይ ለመጣው ፈተና ግንባር ቀደም የመከራው ተካፋይ መሆንዎ ቢታወቅም ልዑል እግዚአብሔር ፈቃዱ ሆኖ ኃዘንዎና ድካምዎን ተቀብሎ የሕማማቱን ወራት አሳልፎ ለበዓለ ትንሣኤው ስላደረሰዎ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ስም እንኳን አደረሰዎ እላለሁ።

ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን፤

ይህ ዕለት ቤተ ክርስቲያን ታላቁን የምሥራች ያበሰረችበት ኃዘንን ጨርሶ የሚያጠፋ የደስታ ስብከት በመላዕክት አንደበት የተሰበከበት ታላቅ ቀን ነው።ከመላእክት ጋር በዓል እያከበርን ከመላእክት ቃል ሦስተኛውን የደስታ ዜና “ለምንት ተኃሥሣሁ ለሕያው ምስለ ምውታን ተንሥአ ኢሀሎ ዝየሰ፤ሕያውን ከሙታን ጋር ስለምን ትፈልጉኛላችሁ ተነሥቷል በዚህ የለም”ሉቃ24፥5 ብለው አይሁድ የሚፈሩትን ፣ እኛ ግን ልንሰማው ስንጠባበቀው የነበረውን ታላቅ ደስታ የሰማንበት ቀን በመሆኑ ደስታችን ዕጥፍ ድርብ ነው።መላዕክት የነገሯቸው ሴቶች ሂደው ትንሣኤውን ካወሩላቸው በኋላ በደቀ መዛሙርቱ መካከል የነበረው ሹክሹክታ “በእውነት ጌታ ተነሥቷል”
የሚለው ነበር ።እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ የትንሣኤው ምስክሮች የሚሆኑ ናቸውና በሦስት ነገር ትንሣኤውን አይተው እንዲያረጋግጡ አድርጓቸዋል ።

1. ከመላእክት አንደበት የመላእክትን ምስክርነት ሰምተው፤
2. ወደ መቃብሩ ገብተው መግነዙ ለብቻው ተጠቅሎ አንዱ በራስጌ አንዱ በግርጌ ወድቆ አይተው፤
3. በጉባኤ ተገኝተው አስቀድሞ በገሊላ ከዚያም በአግብኦተ ግብርና በጥብርያዶስ መነሳቱን ስለአዩ ነው።ከዚያም በተረዳ ነገር የሐዋርያትን ዐይን ዐይን አድርገን ለዘለዓለም “በእውነት ጌታ ተነሥቷል ” እያልን ስንመሰክር እንኖራለን ።

ይሁን እንጂ ትንሣኤውን እያከበርን ትንሣኤ ልቡና ያልተደረገለት ሰው እንዳይኖር ቅዱስነትዎ ጠንካራ ተግሣጽና ምዕዳን እንዲሰጡበት በታላቅ ትህትና ሳልጠቁም አላልፍም ። ዘመኑ የትንሣኤ ነው።ወቅቱ ከሲኦል ወደ ገነት የተሸጋገረበት የመሻገር ዘመን ነው።ትንሣኤ ልቡና ሳይኖር ትንሣኤን ማክበሩ፣ክፋት ወደ በጎነት ሳይሻገሩ”ክርስቶስ ፋሲካችን ” ነው ብሎ መናገር ምን ሊጠቅም ይችላል?

ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን

ያለፈው ወቅት ቤተ ክርስቲያን ከውስጥና ከውጭ በሚፈልቁ ብዙና ብዙ የፈተና ማዕከል ተከባ የተጨነቀችበት ወቅት ነበር ።ቅዱስነትዎ ፈተናውን በትዕግሥትና በጥበብ እንዲሁም ቆራጥና በሳል አመራር በመስጠትዎ እስከ አሁን ጸንተን የቆምን ቢሆንም ነፋሱም መንፈሱን፣ጎርፉም መጉረፉን አቁሟል ማለት አይቻልም ።ስልቱን እየለዋወጠ የሚመጣብንን ብርቱ ፈተና በኅሊና ሞት ውስጥ ሆነን፣በሥጋ ምኞት መቃብር ውስጥ ተቀብረን ማሸነፍ እንችልምና ከወደቅንበት የራስን ጥቅም የማሳደድ አዚም ወጥተን የቤተ ክርስቲያንን ህልውና ሊያጸና የሚችለውን ሥራ እያስቀደምን ማገልገል የሁላችንም ውሳኔ መሆን አለበት።

ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን

ቅዱስነትዎ ቤተ ክርስቲያን ዘመኑ ካመጣው ክፉ በሽታ ከዘረኝነት፣ከሙስናና ከሌላም መጥፎ ጠባይ ተላቃ በእውነተኛው የሐዋርያት መንገድ ስትሔድ ማየት እንደሚፈልጉ ከበዓለ ሢመትዎ ጀምሮ ባስተላለፏቸው ትምህርቶችዎና በዚህ ቅዱስ መንበር ከተቀመጡ በኋላ በሠሯቸው ሥራዎች ማረጋገጥ ይቻላል ።
ነገር ግን ምኞትዎ ተሳክቶ ሀሳብዎ ተፈጽሞ ለማለት ስንናፍቅ በዘመድና በገንዘብ ፍቅር የወደቀው፣ሹመትና ጥቅማ ጥቅም የሚያስጨንቀው ፣የፓለቲካና የጎሣን ጉዳይ ከሃይማኖታዊ ጉዳዮች በላይ አጀንዳ የሚያደርገው በመብዛቱ ቅዱስነትዎ የተመኙትን ያኽል ተሳክቷል ማለት አይቻልም። ጥሪያችን ከሐዋርያት ጋር የትንሣኤው ምስክሮች እንሆን ዘንድ ነው።የሐዋ.ሥራ 1፥22 ሆኖም የትንሣኤው ምስክሮች ለመሆን አስቀድመን ትንሣኤ ልቡና እንዲኖረን ለማድረግ ዛሬም ጸሎትዎ፣ጥበብና ማስተዋል ያልተለየው መመሪያዎ ወሳኝነት አለው።

ክርስቶስ ፋሲካችን ነው ስንል በትክክል በእርሱ ቁስል የተፈጠረውን በእርሱ ፋሲካነት የተሻገርን መሆናችንን አምነን በልማድና ለሰው ይምሰል ከመታየትና ከማስመሰል መራቅ አለብን።ነቅተውና ተግተው ይጠብቁ የነበሩ ደቀ መዛሙርቱ በትንሣኤው ሌሊት “ተነሥቷል “የሚለውን ዜና የሰሙት እንዲሁ በስንፍናና በግዴለሽነት እንዳልሆነ ሁላችንም የምናውቀው ሐቅ ነው። ከእነርሱ መካከል ሌሊቱን ሙሉ ግርማ ሌሊቱ ሳያስፈራራቸው የአይሁድ ጭካኔ ሳያስደነግጣቸው ወደ መቃብሩ ሲመላለሱ ያደሩ ነበሩ።አምላካችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተያዘበት ጊዜ ጀምሮ ምግብ ሳይቀምሱ የሚጠባበቁም ነበሩ። የትንሣኤውን ብርሃን ማየት”ተነሥቷል በዚህ የለም”የሚለውን የምሥራች ሰምቶ መቃብሩ ባዶ መሆኑን አይቶ ለማመን እንደ መቃብር ያለ ታላቅ ምሥጢር የለም።ሰማያት ተከፍተው አምላካችን ክርስቶስ በአብ ቀኝ ተቀምጦ ከማየት በፊት መቃብር ተከፍቶ ሰበኑ ተጠቅልሎ ክርስቶስም በብርሃን ተከቦ ማየት ይቀድማል ።ነገር ግን ያለ ብርቱ ጥረት ሰማያዊ ተስፋ የሚገኝ ባለመሆኑ በዋዛና በፈዛዛ የኖርንባቸው ያለፉትን ዘመናት ትተን ሁላችንም ተግተንና ነቅተን ለሕዝባችን የምንነግረው የምሥራች የሞላበት ዘመን እንዲሰጠን የቅዱስነትዎን መመሪያ አክብረን መሥራት የውዴታ ግዴታችን መሆን አለበት።

ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን

እንደ ተቃዋሚዎችን ሩጫ ቢሆን እዚህ ቀን ላይ መድረስ ለኛ ከባድ የነበረ ቢሆንም በቅዱስነትዎ ጸሎትና ቡራኬ በእግዚአብሔር ቸርነት እዚህ ደርሰናልና ከዚህ በኋላም ቅድስት ሀገራችን ኢትዮጵያ ሰላሟ ጸንቶ፣ አንድነቷ ተረጋግቶ፣ጥንታዊትና ሐዋርያዊት ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን አንድ መንበር፣አንድ ሲኖዶስ፣አንድ ፓትርያርክ ያላት ፍጹም አንድነቷ ከሁሉ በላይ የሆነች ቤተ ክርስቲያን ከአባቶቻችን እጅ እንደተቀበልን እኛም ለሚመጣው ትውልድ አውርሰን
እንድናልፍ አምላከ አበው እግዚአብሔር ይፍቀድልን እያልሁ በድጋሜ ቅዱስ አባታችን ለበዓለ ትንሣኤው እንኳን አደረሰዎ እላለሁ።

“የቅዱስነትዎ ቡራኬ አይለየኝ”

አባ አብርሃም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ሚያዝያ ፱ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የትንሣኤ በዓልን ምክንያት የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር ተካሔደ። Link to: የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የትንሣኤ በዓልን ምክንያት የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር ተካሔደ። የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የትንሣኤ በዓልን ምክንያት የእንኳን... Link to: ቅዱስነታቸው በሰበታ ጌተሰማኒ ጠባባት ገዳም ከሚገኙ ሕጻናት ጋር የፋሲካን በዓል አከበሩ። Link to: ቅዱስነታቸው በሰበታ ጌተሰማኒ ጠባባት ገዳም ከሚገኙ ሕጻናት ጋር የፋሲካን በዓል አከበሩ። ቅዱስነታቸው በሰበታ ጌተሰማኒ ጠባባት ገዳም ከሚገኙ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top