የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

በሰሜን አሜሪካን የሚገኘው ዳግማዊ ደብረ ሊባኖስ ቅዱስ ያሬድና አቡነ ፊሊጶስ ገዳምና የአብነት ትምህርት ቤት ከስልሳ በላይ ታዳጊ ወጣቶችን በመንፈሳዊ የትምህርት ዘርፍ እያሰለጠነ ነው።

June 21, 2023

ሰኔ ፲፭ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም
*****
ሰሜን አሜሪካን ኪንግ ጆርጅ ቨርጂኒያ
“””””””””””””””””””””””””””””””””””

በገዳሙ አማርኛ ቋንቋ ፣ግዕዝ፣ውዳሴ ማርያም፣ የቅዳሴ ትምህርት እና ሌሎችም ኮርሶች ይሰጣሉ።

በሰሜን አሜሪካን ቨርጂኒያ ግዛት ኪንግ ጆርጅ ካውንቲ የሚገኘው ዳግማዊ ደብረ ሊባኖስ ቅዱስ ያሬድና አቡነ ፊሊጶስ ገዳም አንድ መቶ ሃያ ተማሪዎችን በሁለት ዙር በመቀበል በልዩልዩ መንፈሳዊ ትምህርት ዘርፎች ማስተማር ጀመረ።

ገዳሙ በአማርኛ ቋንቋ፣በግዕዝ፣በውዳሴ ማርያም፣ በቅዳሴትምህርት፣በበገና፣በክራር፣በከበሮ፣በኮምፒዩተርና በቅዱሳት ሥዕላት አሳሳል ሥልቶች ዙሪያ ሥልጠናው የሚሰጥ ሲሆን በአብነት ትምህርት ዘርፍ አሉ የተባሉ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ትምህርቱን እንዲሰጡ በማድረግ ውጤታማ ሥራ በማከናወን ላይ ይገኛል።

አብነት ትምህርት ቤቱ በሰሜን አሜሪካን ከፍ ሲል በተጠቀሱ የትምህርት አይነቾች ትምህርት መስጠት በመጀመሩ ወላጆች በከፍተኛ ሁኔታ ደስታቸውን መግለጽ ገዳሙ በዚህ ጊዜ የአብነት ትምህርት መስጠት በመጀመሩ ልጆቻቸው ሃይማኖታቸውን እንዲያውቁ፣ ለሃይማኖታቸው ፍቅር እንዲኖራቸው፣ ከማድረግ ባለፈ ተተኪ ወጣት መምህራንና ምሁራንን ፨ሰሜን አሜሪካን ለማግኘት የሚያስችል በመሆኑ ደስታቸን እጥፍ ድርብ ነው ብለዋል።

አያይዘውም በሰለጠነው ዓለም ዙሪያ የተለያዩ ባህሎችን በምታስተናግደው አሜሪካን ልጆች ሃይማኖታቸውን፣ ወግና ሥርዓታቸውን አውቀው በሁሉም ዘርፍ የተዋጣለት ስብዕና የተላበሱ እንዲሆኑ ይህንን የመሰለ መንፈሳዊ ተቋም በእጅጉ እንደሚያስፈልግና አገልግሎቱን የበለጠ አጠናክሮ መቀጠል ይቻል ዘንድ ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንደሚያስፈልገው የተማሪዎች ወላጆች በሰጡት አስተያጀት ጨምረው ገልጸዋል።

ገዳሙ በቀጥታ ከሚሰጠው የገጽ ለገጽ ትምህርት በተጨማሪ ዘመኑ ባፈራቸው ቴክኖሎጂዎች አማካኝነት የኦንላይን ትምህርት ለበርካታ ተማሪዎች በመስጠት ውጤት እያስመዘገበ የሚገኝ ሲሆን በአሌክሳንድሪያ በገዛው ዴይኬርና አካዳሚ ውስጥም በየሳምንቱ የመንፈሳዊ ትምህርት ከሰባ ለሚበልጡ ታዳጊዎች በመስጠት ቴክኖሎጂና እድገት በሚያስከትለው ጣጣ ልጆች ሃይማኖታቸውን ከማወቅ ውጪ እንዳይሆኑ ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ ይገኛል።

ገዳሙ ወደፊት የመማሪያ ፣የመኝታና የመመገቢያ ክፍሎችን አጠቃሎ የያዘ ባለ ሁለት ወለል ሕንጻ በማስገንባት የአብነት ትምህርት ቤቱን ለማስፋፋትና በርካታ ተማሪዎችን በማፍራት በሰሜን አሜሪካን የስብከተወንጌልና የመንፈሳዊ አገሎግሎት እንዲስፋፋ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የገዳሙ ኃላፊ መልአከ ጥበባት አባ ገብርኤል ገልጸዋል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ/ም የስብከተ ወንጌል እና የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ የጋራ የአገልግሎት ሥምሪት ሥልጠና ተከናወነ። Link to: የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ/ም የስብከተ ወንጌል እና የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ የጋራ የአገልግሎት ሥምሪት ሥልጠና ተከናወነ። የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ/ም የስብከተ ወንጌል እና የሰበካ... Link to: የምሥራቅ አውስትራሊያና ኒውዚላንድ ሀገረ ስብከት በጦርነት ጉዳት ለደረሰባቸው አብያተክርስቲያናት ርዳታ ሰጠ። Link to: የምሥራቅ አውስትራሊያና ኒውዚላንድ ሀገረ ስብከት በጦርነት ጉዳት ለደረሰባቸው አብያተክርስቲያናት ርዳታ ሰጠ። የምሥራቅ አውስትራሊያና ኒውዚላንድ ሀገረ ስብከት...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top