የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱሳት መጻሕፍትን በአእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን የፈጠራ ባለቤትነት መብት ተመዘገበ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱሳት መጻሕፍትን በአእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን የፈጠራ ባለቤትነት መብት ተመዘገበ። የምዝገባ ሰርተፍኬት የተሰጠው ለስምንቱ ብሔረ ኦሪት ከዘፍጥረት እስከ መጽሐፈ ሩት ላለው ነጠላ ትርጉም መሆኑ ታውቋል።

ይህንን ሥራ ለማከናወን ከቅዱስ ሲኖዶስ ኃላፊነት የተቀበለው ኮሚቴና ኮሚቴውን በመምራት ላይ የሚገኙት ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የደቡብና ደቡብ ምሥራቅ ትግራይ፣የቤተ መጻሕፍት ወመዘክርና የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ እና የኮሚቴው ዋና አስተባባሪ መ/ሰ አባ ቃለጽድቅ ሙሉጌታ እያደረጉት ላለው ውጤታማ እንቅስቃሴ ሊመሰገኑ ይገባቸዋል።